መዝሙር 139 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 139:1-24

መዝሙር 139

ሁሉን ዐዋቂ አምላክ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ መረመርኸኝ፤

ደግሞም ዐወቅኸኝ።

2አንተ መቀመጤንና መነሣቴን ታውቃለህ፤

የልቤንም ሐሳብ ገና ከሩቁ ታስተውላለህ።

3መሄድ መተኛቴን አጥርተህ ታውቃለህ፤

መንገዶቼንም ሁሉ ተረድተሃቸዋል።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ገና ቃል ከአንደበቴ ሳይወጣ፣

እነሆ፤ አንተ ሁሉንም ታውቃለህ።

5አንተ ከኋላም ከፊትም ዙሪያዬን ከለልኸኝ፤

እጅህንም በላዬ አደረግህ።

6እንዲህ ያለው ዕውቀት ለእኔ ድንቅ ነው፤

ልደርስበትም የማልችል ከፍ ያለ ነው።

7ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ?

ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?

8ወደ ሰማይ ብወጣ፣ አንተ በዚያ አለህ፤

መኝታዬንም በሲኦል139፥8 አንዳንድ ትርጕሞች በጥልቁ ውስጥ ይላሉ። ባደርግ በዚያ ትገኛለህ።

9በንጋት ክንፍ ተነሥቼ ብበርር፣

እስከ ባሕሩ ዳርቻ መጨረሻ ብሄድ፣

10በዚያም ቢሆን እጅህ ትመራኛለች፤

ቀኝ እጅህም አጥብቃ ትይዘኛለች።

11እኔም፣ “ጨለማው በርግጥ ይሰውረኛል፤

በዙሪያዬ ያለውም ብርሃን ሌሊት ይሆናል” ብል፣

12ጨለማ የአንተን ዐይን አይዝም፤

ሌሊቱም እንደ ቀን ያበራል፤

ጨለማም ብርሃንም ለአንተ አንድ ናቸውና።

13አንተ ውስጣዊ ሰውነቴን ፈጥረሃልና፤

በእናቴም ማሕፀን ውስጥ አበጃጅተህ ሠራኸኝ።

14ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤

ሥራህ ድንቅ ነው፤

ነፍሴም ይህን በውል ተረድታለች።

15እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፣

ዐጥንቶቼ ከአንተ አልተደበቁም፤

በምድር ጥልቀት ውስጥ በጥበብ በተሠራሁ ጊዜ፣

16ዐይኖችህ ገና ያልተበጀውን አካሌን አዩ፤

ለእኔ የተወሰኑልኝም ዘመናት፣

ገና አንዳቸው ወደ መኖር ሳይመጡ፣

በመጽሐፍ ተመዘገቡ።

17አምላክ ሆይ፤ ለእኔ ያለህ ሐሳብ እንዴት ክቡር ነው!

ቍጥሩስ ምንኛ ብዙ ነው!

18ልቍጠራቸው ብል፣

ከአሸዋ ይልቅ ይበዙ ነበር።

ተኛሁም ነቃሁም፣

ገና ከአንተው ጋር ነኝ።

19አምላክ ሆይ፤ ክፉዎችን ብትገድላቸው ምናለበት!

ደም የተጠማችሁ ሰዎች ሆይ፤

ከእኔ ራቁ!

20ስለ አንተ በክፋት ይናገራሉና፤

ጠላቶችህም ስምህን በከንቱ ያነሣሉ።

21እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚጠሉህን አልጠላምን?

በአንተ ላይ የሚነሡትንስ አልጸየፍምን?

22በፍጹም ጥላቻ ጠልቻቸዋለሁ፤

ባላጋራዎቼም ሆነዋል።

23እግዚአብሔር ሆይ፤ መርምረኝ፤ ልቤንም ዕወቅ፤

ፈትነኝ፤ ሐሳቤንም ዕወቅ፤

24የክፋት መንገድ በውስጤ ቢኖር እይ፤

በዘላለምም መንገድ ምራኝ።

Священное Писание

Забур 139:1-14

Песнь 139

1Дирижёру хора. Песнь Давуда.

2Избавь меня, Вечный, от злых людей,

сохрани меня от жестоких.

3Они замышляют зло в сердце,

постоянно готовы к войне.

4Изощряют свой язык, как змея;

у них на губах яд гадюки. Пауза

5Сохрани меня, Вечный, от рук нечестивых,

огради от жестоких,

желающих поколебать мои стопы.

6Высокомерные спрятали силки для меня и петли,

разложили сеть по дороге,

расставили для меня западню. Пауза

7Я сказал Вечному: «Ты – мой Бог;

услышь голос моих молений, Вечный!

8Владыка Вечный, сила моего спасения,

Ты прикрыл мою голову в день сражения.

9Вечный, не исполняй желания нечестивых,

не дай успеха их замыслу,

чтобы они не возгордились». Пауза

10Пусть падёт на голову окруживших меня несчастье,

которое вызвали их собственные уста.

11Пусть падут на них горящие угли;

пусть будут они повержены в огонь,

в глубокую пропасть, откуда не подняться им.

12Пусть не утвердится на земле злоязычный человек;

пусть зло преследует жестоких на погибель им.

13Я знаю, что Вечный даст правосудие бедным

и заступится за нищих.

14Поистине, праведные будут славить Твоё имя;

честные будут жить в Твоём присутствии.