መዝሙር 125
እግዚአብሔር የሚታመኑበትን ይጠብቃል
መዝሙረ መዓርግ።
1በእግዚአብሔር የሚታመኑ፣
ሳትናወጥ ለዘላለም እንደምትኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው።
2ተራሮች ኢየሩሳሌምን እንደ ከበቧት፣
ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣ እግዚአብሔር በሕዝቡ ዙሪያ ነው።
3ጻድቃን እጃቸውን ለክፋት እንዳያነሡ፣
የክፉዎች በትረ መንግሥት፣
ለጻድቃን በተመደበች ምድር ላይ አያርፍም።
4እግዚአብሔር ሆይ፤ መልካም ለሆኑ፣
ልባቸውም ለቀና መልካም አድርግ።
5ወደ ጠማማ መንገዳቸው የሚመለሱትን ግን፣
እግዚአብሔር ከክፉ አድራጊዎች ጋር ያስወግዳቸዋል።
በእስራኤል ላይ ሰላም ይውረድ።
Psalm 125
A song of ascents.
1Those who trust in the Lord are like Mount Zion,
which cannot be shaken but endures forever.
2As the mountains surround Jerusalem,
so the Lord surrounds his people
both now and forevermore.
3The scepter of the wicked will not remain
over the land allotted to the righteous,
for then the righteous might use
their hands to do evil.
4Lord, do good to those who are good,
to those who are upright in heart.
5But those who turn to crooked ways
the Lord will banish with the evildoers.
Peace be on Israel.