መዝሙር 115 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 115:1-18

መዝሙር 115

አንዱ እውነተኛው አምላክ

115፥4-11 ተጓ ምብ – መዝ 135፥15-20

1ለእኛ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለእኛ ሳይሆን፣

ስለ ምሕረትህና ስለ እውነትህ፣

ለስምህ ክብርን ስጥ።

2አሕዛብ፣ “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ?

3አምላካችንስ በሰማይ ነው፤

እርሱ ደስ የሚለውን ያደርጋል።

4የእነርሱ ጣዖታት ግን የሰው እጅ የሠራቸው፣

ብርና ወርቅ ናቸው።

5አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፣

6ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

አፍንጫ አላቸው፤ አያሸትቱም፤

7እጅ አላቸው፤ አይዳስሱም፤

እግር አላቸው፤ አይሄዱም፤

በጕሮሯቸውም ድምፅ አይፈጥሩም።

8እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

9የእስራኤል ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

10የአሮን ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

11እናንተ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

12እግዚአብሔር ያስበናል፤ ይባርከናልም፤

እርሱ የእስራኤልን ቤት ይባርካል፤

የአሮንንም ቤት ይባርካል።

13እግዚአብሔርን የሚፈሩትን ሁሉ፣

ትልቁንም ትንሹንም ይባርካል።

14እግዚአብሔር እናንተንና ልጆቻችሁን፣

በባርኮቱ ያብዛችሁ።

15ሰማይንና ምድርን በፈጠረ፣

በእግዚአብሔር የተባረካችሁ ሁኑ።

16ሰማየ ሰማያት የእግዚአብሔር ናቸው፤

ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።

17እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑት የሞቱት አይደሉም፤

ወደ ዝምታው ዓለም የሚወርዱም አይደሉም።

18ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣

እግዚአብሔርን የምንባርክ እኛ ነን።

እግዚአብሔር ይመስገን።115፥18 ዕብራይስጡ ሃሌ ሉያ ይላል።

Священное Писание

Забур 115:1-10

Песнь 115Песнь 115 В тексте оригинала песни 114 и 115 объединены в одну песнь.

1Я верил, даже когда говорил115:1 Или: «поэтому я и говорил».:

«Я сильно сокрушён».

2В исступлении я сказал:

«Все люди – лжецы».

3Чем воздам я Вечному

за всю Его доброту ко мне?

4Возолью вино в жертву Вечному,

возблагодарю Его за спасение моё.

5Исполню мои обеты Вечному

перед всем Его народом.

6Дорога в глазах Вечного

смерть верных Ему.

7Вечный, истинно я – Твой раб;

Я – Твой раб и сын Твоей рабыни.

Ты освободил меня от цепей.

8Принесу Тебе жертву благодарности

и призову имя Вечного.

9Исполню мои обеты Вечному

перед всем Его народом,

10во дворах дома Вечного,

посреди тебя, Иерусалим!

Славьте Вечного!