መክብብ 11 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

መክብብ 11:1-10

እንጀራ በውሃ ላይ

1እንጀራህን በውሃ ላይ ጣል፤

ከብዙ ቀን በኋላ መልሰህ ታገኘዋለህና።

2ሀብትህን ሰባት ቦታ፣ እንዲያውም ስምንት ቦታ ከፍለህ አስቀምጥ፤

በምድሪቱ ላይ የሚመጣውን ጥፋት አታውቅምና።

3ደመናት ውሃ ካዘሉ፣

በምድር ላይ ዝናብን ያዘንባሉ፤

ዛፍ ወደ ደቡብም ሆነ ወደ ሰሜን ቢወድቅ፣

በወደቀበት ቦታ በዚያ ይጋደማል።

4ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፤

ደመናትንም የሚያይ አያጭድም።

5የነፋስን መንገድ እንደማታውቅ፣

ሕይወት ወይም መንፈስ በእናት ማሕፀን ውስጥ ወደሚገኘው አካል እንዴት እንደሚገባም11፥5 ወይም አካል በእናት ማሕፀን ውስጥ እንዴት እንደሚሠራ እንደማታውቅ ሁሉ እንደማታውቅ ሁሉ፣

ሁሉን ሠሪ የሆነውን፣ የእግዚአብሔርን ሥራ

ማስተዋል አትችልም።

6ጧት ላይ ዘርህን ዝራ፤

ማታም ላይ እጅህ ሥራ አይፍታ፤

ይህ ወይም ያ፣

ወይም ሁለቱ መልካም ይሁኑ፣

የቱ እንደሚያፈራ አታውቅምና።

ወጣት ሳለህ ፈጣሪህን ዐስብ

7ብርሃን መልካም ነው፤

ፀሓይንም ማየት ለዐይን ደስ ያሰኛል።

8ሰው ምንም ያህል ብዙ ዓመት ቢኖር፣

በእነዚህ ሁሉ ይደሰት፤

ነገር ግን ጨለማዎቹንም ቀናት ያስብ፤

እነርሱ ይበዛሉና፤

የሚመጣውም ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።

9አንተ ወጣት በወጣትነትህ ጊዜ ደስ ይበልህ፤

በወጣትነትህም ዘመን ልብህ ደስ ያሰኝህ፤

የልብህን መንገድ፣

ዐይንህ የሚያየውንም ሁሉ ተከተል፤

ነገር ግን ስለ እነዚህ ነገሮች ሁሉ፣

እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንደሚያመጣህ ዕወቅ።

10ስለዚህ ጭንቀትን ከልብህ አርቅ፤

ክፉ ነገርንም ከሰውነትህ አስወግድ፤

ወጣትነትና ጕብዝና ከንቱ ናቸውና።

Bibelen på hverdagsdansk

Prædikerens Bog 11:1-10

Vejledning for vise

1Invester vidt og bredt, du skal nok få udbytte af det med tiden. 2Fordel dine investeringer på mange hænder, for du ved ikke, hvilke ulykker der kan ske.

3Når skyerne er tunge og sorte, kommer der altid regn. Et træ kan falde til den ene eller anden side, men der er ingen tvivl om, at det vil ramme jorden. 4Den, der venter på det helt ideelle vejr, får hverken sået eller høstet. 5Gud har skabt alle ting, og hans handlinger går over vores forstand, ligesom vi ikke forstår, hvordan vinden blæser, eller hvordan fosteret formes i moderens liv. 6Du bør plante meget forskelligt, for du ved ikke, om det ene eller det andet lykkes, ja, måske lykkes det hele.

Et råd til de unge—husk at leve, mens du gør det

7Det er rart at kunne nyde livet. 8Uanset hvor længe du lever, så vær taknemmelig for hver eneste dag, du kan nyde. Når du først er død, bliver alt til mørke og håbløshed.

9Glæd dig og nyd livet i din ungdom. Følg dit hjerte og brug dine evner. Men husk, at du en dag skal stå til regnskab over for Gud. 10Spild ikke tiden med bekymringer og problemer, for barndom og ungdom forsvinder som dug for solen.