መክብብ 1 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

መክብብ 1:1-18

ሁሉም ነገር ከንቱ ነው

1በኢየሩሳሌም የነገሠው፣ የዳዊት ልጅ፣ የሰባኪው ቃል1፥1 ወይም የጕባኤ መሪ፤ እንዲሁም በ2 እና 12

2ሰባኪው፣

“ከንቱ፣ ከንቱ፣

የከንቱ ከንቱ፤

ሁሉም ነገር ከንቱ ነው” ይላል።

3ከፀሓይ በታች ከሚለፋበት ተግባር ሁሉ፣

ሰው ምን ትርፍ ያገኛል?

4ትውልድ ይሄዳል፤ ትውልድ ይመጣል፤

ምድር ግን ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች።

5ፀሓይ ትወጣለች፤ ትጠልቃለችም፤

ወደምትወጣበትም ለመመለስ ትጣደፋለች።

6ነፋስ ወደ ደቡብ ይነፍሳል፤

ወደ ሰሜንም ይመለሳል፤

ዞሮ ዞሮ ይሄዳል፤

ዘወትርም ወደ ዑደቱ ይመለሳል።

7ወንዞች ሁሉ ወደ ባሕር ይፈስሳሉ፤

ባሕሩ ግን ፈጽሞ አይሞላም፤

ወንዞች ወደ መጡበት ስፍራ፣

ወደዚያ እንደ ገና ይመለሳሉ።

8ሰው መናገር ከሚችለው በላይ፣

ነገሮች ሁሉ አድካሚ ናቸው፤

ዐይን ከማየት አይጠግብም፤

ጆሮም በመስማት አይሞላም።

9የነበረው ነገር እንደ ገና ይሆናል፤

የተደረገውም ተመልሶ ይደረጋል፤

ከፀሓይ በታች ምንም አዲስ ነገር የለም።

10ማንም፣ “እነሆ፤ ይህ አዲስ ነገር ነው!”

ሊል የሚችለው አንዳች ነገር አለን?

ቀድሞውኑ በዚሁ የነበረ ነው፤

ከእኛ በፊት የሆነ ነው።

11የቀድሞ ነገሮች መታሰቢያ የላቸውም፤

ወደ ፊት የሚመጡትም ቢሆኑ፣

ከእነርሱ በኋላ በሚተኩት አይታወሱም።

ጥበብ ከንቱ ነው

12እኔ ሰባኪው፣ በኢየሩሳሌም የእስራኤል ንጉሥ ነበርሁ። 13ከሰማይ በታች የተደረገውን ሁሉ በጥበብ ለማጥናትና ለመመርመር ራሴን አተጋሁ፤ አምላክ በሰዎች ላይ የጫነው እንዴት ያለ ከባድ ሸክም ነው! 14ከፀሓይ በታች የተደረገውን ነገር ሁሉ አየሁ፤ ሁሉም ከንቱ፣ ነፋስንም እንደ መከተል ነው።

15የተጣመመው ሊቃና አይችልም፤

የሌለም ነገር ሊቈጠር አይችልም።

16እኔም በልቤ፣ “እነሆ፤ ከእኔ በፊት በኢየሩሳሌም ከገዙት ከማንኛቸውም ይልቅ ታላቅ ሆኛለሁ፤ ጥበብም በዝቶልኛል፤ በብዙ ጥበብና ዕውቀት ተመክሮም ዐልፌአለሁ” አልሁ። 17ከዚያም የጥበብንና የእብደትን፣ የሞኝነትንም ነገር ለመገንዘብ ራሴን አተጋሁ፤ ይህም ነፋስን እንደ መከተል መሆኑን ተረዳሁ።

18ጥበብ ሲበዛ፣ ትካዜ ይበዛልና፤

ዕውቀት ሲጨምርም ሐዘን ይበዛል።

Korean Living Bible

전도서 1:1-18

덧없는 인생

1이것은 다윗의 아들이며 예루살렘의 왕인 전도자 솔로몬의 말이다.

2전도자는 말한다. “모든 것이 헛되고 무가치하며 의미가 없으니 아무것도 소중한 것이 없구나.”

3사람이 평생 동안 수고하여 얻는 것이 무엇인가?

4세대는 왔다가 가지만 1:4 또는 ‘내가 사는 것을 한하였노니’세상은 변함이 없구나.

5해는 떴다가 져서 그 떴던 곳으로 빨리 되돌아가며

6바람은 남으로 불고 북으로 불다가 돌고 돌아 다시 돌아가고

7모든 강물이 바다로 흘러도 바다를 다 채우지 못하며 그 물은 강으로 되돌아가 다시 바다로 흐른다.

8만물의 피곤함을 이루 다 말할 수 없으니 사람이 아무리 많은 것을 보고 들어도 만족함을 모르는구나.

9전에 있던 것도 다시 있을 것이며 이미 한 일도 다시 하게 될 것이니 세상에는 아무것도 새로운 것이 없다.

10“보라, 이것은 새 것이다” 하고 말할 수 있는 게 무엇인가? 그것은 우리가 태어나기 전에 오래 전부터 있었던 것이다.

11우리가 과거에 일어난 일을 기억하지 않으니 앞으로 올 세대들도 우리 시대에 일어난 일을 기억하지 않으리라.

세상적인 지혜와 지식의 무상함

12나 전도자는 예루살렘에서 이스라엘의 왕이 되어

13정신을 집중하고 지혜를 모아 이 세상의 모든 일을 깊이 연구하고 살펴보았으니 하나님이 주신 인간의 운명은 괴롭고 고통스러운 것이다.

14내가 세상에서 되어지는 모든 일을 보니 다 허무하여 바람을 잡으려는 것 같다.

15비틀어진 것은 바로잡을 수 없으며 없는 것은 셀 수가 없다.

16나는 혼자 이런 생각을 해 보았다. “나는 나보다 먼저 예루살렘을 다스린 그 어떤 사람보다 더 위대하고 지혜로우며 많은 지혜와 지식을 쌓았다.”

17그 후에 내가 지혜와 미치는 것과 어리석음에 대해서 알고자 정신을 쏟았으나 이것도 역시 바람을 잡으려는 것임을 깨달았다.

18지혜가 많으면 번민이 많고 지식이 많으면 근심이 많은 법이다.