መሳፍንት 13 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 13:1-25

የሳምሶን መወለድ

1እስራኤላውያን እንደ ገና በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸሙ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያን እጅ አርባ ዓመት እንዲገዙ አሳልፎ ሰጣቸው።

2ማኑሄ የተባለ ከዳን ወገን የተወለደ አንድ የጾርዓ ሰው ነበረ፤ ሚስቱ መካን ስለ ነበረች ልጅ አልወለደችም። 3የእግዚአብሔርም መልአክ ለሴቲቱ ተገልጦ እንዲህ አላት፤ “እነሆ፤ አንቺ መካን ነሽ፤ ልጅም አልወለድሽም፤ ነገር ግን ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። 4እንግዲህ ተጠንቀቂ፤ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጪ፤ ርኩስ ነገርም አትብዪ፤ 5ምክንያቱም ትፀንሻለሽ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ ልጁ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ ናዝራዊ በመሆን ለእግዚአብሔር የተለየ ይሆናልና፤ እስራኤልንም ከፍልስጥኤማውያን እጅ መታደግ ይጀምራል።”

6ከዚያም ሴቲቱ ወደ ባሏ ሄዳ እንዲህ አለችው፤ “የእግዚአብሔር ሰው ወደ እኔ መጣ፤ የእግዚአብሔር መልአክ የሚመስልና እጅግ የሚያስደነግጥ ነበር። ከየት እንደ መጣ አልጠየቅሁትም፤ እርሱም ስሙን አልነገረኝም፤ 7ነገር ግን፣ ‘ትፀንሻለሽ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲያ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጪ፤ ርኩስ ነገር አትብዪ፤ ልጁም ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ እስኪሞት ድረስ ናዝራዊ በመሆን ለእግዚአብሔር የተለየ ይሆናልና’ ብሎኛል።”

8ከዚያም ማኑሄ፣ “ጌታ ሆይ፤ የሚወለደውን ልጅ እንዴት አድርገን ማሳደግ አንዳለብን እንዲያስተምረን ያ ወደ እኛ የላክኸው የእግዚአብሔር ሰው እንደ ገና እንዲመጣ ታደርግ ዘንድ እለምንሃለሁ” ብሎ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።

9እግዚአብሔርም የማኑሄን ጸሎት ሰማ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ሴቲቱ በዕርሻ ውስጥ ሳለች ተገለጠላት፤ በዚህ ጊዜ ግን ባሏ ማኑሄ አብሯት አልነበረም። 10እርሷም ለባሏ ለመንገር ፈጥና በመሄድ፣ “ባለፈው ጊዜ የተገለጠልኝ ሰው ዛሬም ተገለጠልኝ” አለችው። 11ማኑሄም ተነሥቶ ሚስቱን ተከተላት፤ ሰውየው እንደ ደረሰም፣ “ከሚስቴ ጋር ተነጋግረህ የነበርኸው አንተ ነህ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፤ “አዎን እኔ ነኝ” አለው።

12ማኑሄም፣ “ያልኸው በሚፈጸምበት ጊዜ የልጁ ሕይወት የሚመራው እንዴት ነው? እኛስ ምን ማድረግ አለብን?” ሲል ጠየቀው።

13የእግዚአብሔርም መልአክ እንዲህ አለው፤ “ሚስትህ የነገርኋትን ሁሉ ታድርግ። 14ከወይን ተክል የሚገኝ ማንኛውንም ነገር አትብላ፤ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጣ፤ ርኩስ ነገር አትብላ፤ ያዘዝኋትንም ሁሉ ታድርግ።”

15ከዚያም ማኑሄ የእግዚአብሔርን መልአክ፣ “የፍየል ጠቦት ዐርደን እስክናዘጋጅልህ ድረስ እባክህ ቈይ” አለው።

16የእግዚአብሔርም መልአክ፣ “የግድ ብታቈየኝ እንኳ የምታቀርበውን ማንኛውንም ምግብ አልበላም፤ ነገር ግን የሚቃጠል መሥዋዕት የምታዘጋጅ ከሆነ እርሱን ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። የሚያነጋግረው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አላወቀም ነበር።

17ማኑሄ የእግዚአብሔርን መልአክ፣ “የተናገርኸው ሲፈጸም እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?” በማለት ጠየቀው።

18እርሱም፣ “ስሜ ድንቅ13፥18 ወይም ድንቁ ስለሆነ፣ ለምን ትጠይቀኛለህ?” አለው። 19ማኑሄም የፍየሉን ጠቦት ከእህል ቍርባኑ ጋር ወስዶ በዐለት ላይ ለእግዚአብሔር ሠዋው። ማኑሄና ሚስቱ እያዩ እግዚአብሔር አስደናቂ ነገር አደረገ፤ 20ይኸውም የእሳቱ ነበልባል ከመሠዊያው ወደ ሰማይ ሲወጣ፣ የእግዚአብሔር መልአክ በነበልባሉ ውስጥ ዐረገ። ማኑሄና ሚስቱ ይህን ሲመለከቱ በግንባራቸው መሬት ላይ ተደፉ። 21የእግዚአብሔርም መልአክ ለማኑሄና ለሚስቱ ዳግመኛ ባለመገለጡ፣ ቀደም ሲል የተገለጠላቸው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን ማኑሄ ዐወቀ።

22ሚስቱንም፣ “እግዚአብሔርን ስላየን ያለ ጥርጥር እንሞታለን” አላት።

23ሚስቱ ግን መልሳ እንዲህ አለችው፣ “እግዚአብሔር ሊገድለን ቢፈልግ ኖሮ፣ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህል ቍርባኑን ከእጃችን ባልተቀበለን፤ ደግሞም ይህን ነገር ሁሉ ባላሳየንና እንዲህ ያለውንም ነገር በዚህ ጊዜ ባልነገረን ነበር።”

24ሴቲቱ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ሳምሶን ብላ ጠራችው። ልጁ አደገ፤ እግዚአብሔርም ባረከው፤ 25የእግዚአብሔርም መንፈስ በጾርዓና በኤሽታኦል መካከል ባለው በዳን ሰፈር ሳለ ያነቃቃው ጀመር።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

士师记 13:1-25

参孙的出生

1以色列人又做耶和华视为恶的事,耶和华就把他们交在非利士人手中四十年。

2琐拉城住了一个支派的人,名叫玛挪亚。他妻子不能生养,没有孩子。 3耶和华的天使向那妇人显现,对她说:“你虽然多年不育,但不久你必怀孕生一个儿子。 4所以,你要留心,不可喝淡酒和烈酒,不可吃不洁之物。 5你必怀孕生一个儿子,你不可为他剃头,因为他一出生就要归给上帝做拿细耳人13:5 拿细耳人”参见民数记6:1-8。他要从非利士人手中拯救以色列人。” 6妇人就去对丈夫说:“有一位上帝的仆人向我显现,他的容貌像上帝的天使,非常可畏。我没有问他从哪里来,他也没有把名字告诉我。 7他对我说,‘你必怀孕生一个儿子,所以不可喝淡酒和烈酒,不可吃不洁之物,因为孩子一出生就要献给耶和华,终生做拿细耳人。’”

8玛挪亚向耶和华祈求说:“主啊,求你再派你的仆人到这里来,教我们怎样照顾要出生的孩子。” 9上帝应允了他的祈求。他妻子正坐在田间的时候,上帝的天使再次向她显现。当时她丈夫玛挪亚不在场。 10她赶忙跑去告诉她丈夫说:“那天来的那人又向我显现了。” 11玛挪亚立刻跟随妻子来到那人面前,问他:“那天跟我妻子说话的就是你吗?”他答道:“是我。” 12玛挪亚问道:“你的话应验以后,我们应该怎样抚养这孩子?他该做什么?” 13耶和华的天使说:“你的妻子必须谨记我的一切吩咐。 14她不可吃葡萄树所结的果实,淡酒和烈酒都不可喝,不可吃任何不洁之物。她必须遵行我的一切吩咐。”

15玛挪亚说:“请你留下来,我们要预备一只山羊羔给你吃。” 16当时,玛挪亚仍然不知道那人是耶和华的天使。天使说:“我就是留下来也不会吃你预备的食物。如果你预备燔祭,就把它献给耶和华吧!” 17玛挪亚说:“请告诉我你的名字,当一切应验的时候,我们好向你表达敬意。” 18耶和华的天使说:“何必问我的名字呢?我的名字奇妙难测。” 19于是,玛挪亚就把一只山羊羔和素祭放在磐石上,献给耶和华。就在这时候,天使在玛挪亚和他妻子面前行了一件奇妙的事: 20火焰从祭坛上升起的时候,耶和华的天使也在祭坛的火焰中升上去了。玛挪亚夫妇见状,便俯伏在地。

21耶和华的天使后来没再向玛挪亚和他妻子显现,玛挪亚才知道他是耶和华的天使。 22玛挪亚对妻子说:“我们必死无疑,因为我们看见了上帝。” 23他妻子却说:“如果耶和华要杀我们,祂就不会接受我们的燔祭和素祭了,也不会让我们看见这些事并告诉我们这些话了。”

24后来玛挪亚的妻子生了个儿子,她给孩子取名叫参孙。这孩子渐渐长大,耶和华赐福给他。 25当他在琐拉以实陶之间的玛哈尼·但的时候,耶和华的灵开始感动他。