ሕዝቅኤል 21 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 21:1-32

የቅጣት በትር የሆነችው ባቢሎን

1የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 2“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ ኢየሩሳሌም አዙር፤ በመቅደሱ ላይ ቃል ተናገር፤ በእስራኤል ምድር ላይ ትንቢት ተንብይ፤ 3እንዲህም በል፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እኔ በአንቺ ላይ ተነሥቻለሁ፤ ሰይፌን ከሰገባው እመዝዛለሁ፤ ጻድቁንም፣ ክፉውንም ከአንተ ዘንድ አስወግዳለሁ። 4ጻድቁንም ክፉውንም ስለማስወግድ ሰይፌ ከደቡብ ጀምሮ እስከ ሰሜን ባለው ሕዝብ ሁሉ ላይ ከሰገባው ይመዘዛል። 5ሰይፌን ከሰገባው የመዘዝሁት እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ሕዝቡ ሁሉ ያውቃል፤ እርሱም ወደ ሰገባው አይመለስም።’

6“ስለዚህ የሰው ልጅ ሆይ፤ አቃስት፤ በተሰበረ ልብና በመረረ ሐዘን አቃስት፤ 7እነርሱም፣ ‘ለምን ታቃስታለህ?’ ቢሉህ፣ ‘ስለሚመጣው ክፉ ወሬ ነው፤ ልብ ሁሉ ይቀልጣል፤ እጅም ሁሉ ይዝላል፤ ነፍስ ሁሉ ይደክማል፤ ጕልበትም ሁሉ ውሃ ይሆናል’ በላቸው። እነሆ ይመጣል፤ ይፈጸማልም፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።”

8የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 9“የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤ እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እንዲህ ይላል፤

“ ‘ሰይፍ! ሰይፍ!

የተሳለ የተወለወለም፤

10የተሳለው ሊገድል፣

የተወለወለውም እንደ መብረቅ ሊብረቀረቅ ነው!

“ ‘ታዲያ፣ እንዴት ደስ ሊለን ይችላል? ሰይፉ የልጄን በትረ መንግሥት እንደ ማንኛውም በትር ንቋል።

11“ ‘በእጁ እንዲያዝ፣

ሰይፉ ሊወለወል ተሰጥቷል፤

ገዳዩ በእጁ እንዲጨብጠው፣

ተስሏል፤ ተወልውሏል።

12የሰው ልጅ ሆይ፤ ይህ በሕዝቤ ላይ፣

በእስራኤልም መሳፍንት ሁሉ ላይ መጥቷልና፤

ጩኸት፣ ዋይታም አሰማ።

እነርሱ ከሕዝቤ ጋር በአንድ ላይ፣

ለሰይፍ ተጥለዋል፤

ስለዚህ ደረትህን ምታ።

13“ ‘ፈተና በርግጥ ይመጣል፤ ሰይፉ የናቀው በትረ መንግሥት ዘላቂነት ባይኖረውስ? ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’

14“እንግዲህ፣ የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤

በእጅህም አጨብጭብ፤

ሰይፉ ሁለት ጊዜ፣

ሦስት ጊዜም ይምታ፤

በእጅጉ የሚገድል፣

ለግድያ የሚሆን፣

በየአቅጣጫውም የሚከባቸው ሰይፍ ነው።

15ልብ ሁሉ ይቀልጥ ዘንድ፣

የሚወድቁትም እንዲበዙ፣

በበሮቻቸው ሁሉ፣

የግድያውን ሰይፍ21፥15 ከሰብዐ ሊቃናት ጋር ተመሳሳይ ሲሆን በዕብራይስጡ ግን የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም። አኑሬአለሁ።

ወዮ! እንዲያብረቀርቅ ተወልውሏል፤

ለመግደልም ተመዝዟል።

16ሰይፍ ሆይ፤ በስለትህ አቅጣጫ ሁሉ፣

ወደ ቀኝም፣

ወደ ግራም ቍረጥ።

17እኔም በእጄ አጨበጭባለሁ፤

ቍጣዬም ይበርዳል፤

እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ።”

18የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 19“የሰው ልጅ ሆይ፤ የባቢሎን ንጉሥ ሰይፍ የሚመጣባቸውን የሁለት መንገዶች ካርታ ንደፍ፤ መንገዶቹም ከአንድ አገር የሚነሡ ናቸው፤ መንገዱ ወደ ከተማው በሚገነጠልበት ቦታ ላይ ምልክት አቁም። 20በአሞናውያን ከተማ በረባት ላይ ለሚመጣው ሰይፍ አንደኛውን መንገድ ምልክት አድርግ፤ በይሁዳና በተመሸገችው ከተማ በኢየሩሳሌም ላይ ለሚመጣውም ሰይፍ ሁለተኛውን መንገድ ምልክት አድርግ። 21የባቢሎን ንጉሥ በጥንቈላ ምሪት ለማግኘት በመንታ መንገድ ላይ በሁለቱ ጐዳናዎች መጋጠሚያ ላይ ይቆማል፤ ቀስቶቹን በመወዝወዝ ዕጣ ይጥላል፤ አማልክቱን ያማክራል፤ ጕበትንም ይመረምራል። 22የቅጥር መደርመሻ አምጥቶ እንዲያቆም፣ ለመግደል ትእዛዝ እንዲሰጥ፣ ፉከራ እንዲያሰማ፣ ቅጥር መደርመሻውን በከተሞች በር ላይ እንዲያደርግ፣ የዐፈር ድልድል እንዲያበጅና ምሽግ እንዲሠራ የኢየሩሳሌም ዕጣ በቀኝ እጁ ወጣ። 23ይህም ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን ለገቡት የተሳሳተ ምሪት ይመስላል፤ እርሱ ግን በደላቸውን ያሳስባቸዋል፤ ማርኮም ይዟቸው ይሄዳል።

24“ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እናንተ በምታደርጉት ሁሉ ኀጢአታችሁን በመግለጽ፣ በግልጽም በማመፅ በደላችሁን ስላሳሰባችሁ፣ እንዲህም ስላደረጋችሁ በምርኮ ትወሰዳላችሁ።

25“ ‘አንተ የግፍ ጽዋህ የሞላ፣ የምትቀጣበት ቀን የደረሰ፣ ርኩስና ክፉ የእስራኤል መስፍን ሆይ፤ 26ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ጥምጥምህን አውልቅ፤ ዘውድህን ጣል፤ እንደ ከዚህ በፊቱ አይሆንም፤ ዝቅ ያለው ከፍ ይላል፤ ከፍ ያለውም ዝቅ ይላል። 27ባድማ! ባድማ! ባድማ አደርጋታለሁ፤ የሚገባው ባለ መብት እስከሚመጣ ድረስ እንደ ቀድሞው አትሆንም፤ ለእርሱም ደግሞ እሰጣታለሁ።” ’

28“አንተ የሰው ልጅ ሆይ! እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ስለ አሞናውያንና ስለ ስድባቸው ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ሰይፍ! ሰይፍ!

ሊገድል የተመዘዘ፣

ሊያጠፋ የተጠረገ፣

እንደ መብረቅ ሊያብረቀርቅ የተወለወለ፤

29የታለመልህ የሐሰት ራእይ፣

የተነገረልህ የውሸት ሟርት ቢኖርም፣

የግፍ ጽዋቸው በሞላ፣

ቀናቸው በደረሰ፣

መታረድ በሚገባቸው ክፉዎች፣

ዐንገት ላይ ይሆናል።

30“ ‘ሰይፉን ወደ ሰገባው መልሰው፤

በተፈጠርህበት ምድር፣

በተወለድህበትም አገር፣

በዚያ እፈርድብሃለሁ።

31መዓቴን በላይህ አፈስሳለሁ፤

የቍጣዬንም እሳት አነድድብሃለሁ፣

በጥፋት ለተካኑ፣

ለጨካኞች ሰዎች አሳልፌ እሰጥሃለሁ።

32ለእሳት ማገዶ ትሆናለህ፣

ደምህ በምድርህ ይፈስሳል፣

ከእንግዲህ መታሰቢያ አይኖርህም፤

እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና።’ ”

Japanese Contemporary Bible

エゼキエル書 21:1-32

21

神のさばきの剣であるバビロン

1それから、このようなことばが主からありました。 2「人の子よ、エルサレムに顔を向け、イスラエルとわたしの神殿とに預言しなさい。 3主はこう語る。イスラエルよ。わたしはあなたを攻める。剣を抜き、善人も悪人も区別なく、みな滅ぼす。 4正しい者も生かしてはおかない。南のネゲブから北の国境まで、国中の者をきれいに一掃する。 5すべての国々は、こうしたのが主であるわたしであることを知る。わたしは剣を手にし、このことをやり遂げるまで剣をさやに納めない。

6人の子よ、激しい苦悶のあまり、人々の前で嘆き、うめき声を上げよ。 7どうしたのかと聞かれたら、こう答えよ。『神が恐ろしいことを語ったからだ。そのとおりになったら、どんな勇敢な者も恐怖におののき、意気消沈し、だれのひざも震える。神である主がそう語ったのだ。』あなたは滅びに向かっている。わたしのさばきは成就する。」

8続いて、主のことばがありました。

9-11「人の子よ、このように人々に告げよ。

大虐殺のために、

もう一振りの剣が研ぎすまされている。

それでも、笑い飛ばそうというのか。

あなたよりずっと強い者も滅んでいった。

その剣が今、刑を執行する者の手に渡されている。

12人の子よ、さあ、人目もはばからず泣きわめけ。

その剣で、わたしの民と指導者がみな殺されるからだ。

みな同じように死ぬ。

13こうして、すべての者が試される。

逃れることはできない。」

神である主がこう語るのです。

14「このように預言せよ。

力いっぱい手を打ち鳴らせ。

それから剣を取って、二回、三回と振り回せ。

それこそ彼らが虐殺されるしるしだ。

15彼らを震え上がらせよ。

抜き放たれた剣が、どの家の門口でも光っている。

その鋭い刃先が、人を切り殺そうと、

いなずまのように光っている。

16さあ剣よ、右に左に、思うままに切りまくれ。

17あなたが手を打ち鳴らして預言したように、

主であるわたしがエルサレムを打ちのめして、

わたしの憤りを静めよう。」

18それから、このようなことばが示されました。主はこう語りました。 19-20「人の子よ、地図を作りなさい。その上に、バビロンの王が攻めて来る二つの道を書きつけるのだ。一つはエルサレムに通じる道、もう一つはヨルダン川東岸のラバに向かう道だ。バビロンからの道が二つに別れる地点にしるしをつけておきなさい。 21バビロンの王はその地点で、エルサレムを攻撃しようか、ラバを攻撃しようか、と思案するからだ。彼は占い師を呼んで占わせる。占い師は矢筒から矢を振り出したり、偶像にささげたいけにえの肝を調べたりする(神々から情報を得る、古代の占い法)。 22その結果、エルサレムに向かえ、と言うだろう。彼らは城壁を破壊する兵器を持って、城門めがけて攻めかかり、『皆殺しにしろ』と口々に叫ぶ。また、包囲攻撃用に塔を建て、城壁を乗り越えるためにとりでを築く。 23エルサレムはバビロンの裏切りを理解できない。どうして占い師は、こんな恐ろしい間違いをしでかしたのか。バビロンはユダの同盟国ではないか。エルサレムを守ると約束してくれたではないか。だがバビロンの王には、ユダの民が反逆した時のことしか念頭にないのだ。王はユダを攻め、民を滅ぼす。」

24さらに主は語ります。「あなたがたの罪は何度もあばかれている。人前もはばからず、ぬけぬけと悪を行っているからだ。あなたがたはどこへ行っても、何をしても、悪いことばかりしている。今こそ罰を受ける時だ。 25ああ、悪にまみれたイスラエルの王ゼデキヤよ。あなたの最後の刑罰の日がきた。」

26神である主が語ります。「宝石をちりばめた冠を取り去れ。世の中がひっくり返る。今や、貧しい人が高い地位につき、金持ちが低くされる。 27わたしはユダの王国を根底からくつがえす。たとえ新しい体制が生まれても、それに権威を授ける者が現れるまで、決して国は確立しない。わたしが、その者にあらゆる権威を与えるのだ。

28人の子よ、アモン人にも預言せよ。彼らはわたしの民が苦しんでいた時、それをあざ笑っていた。彼らにこう言え。おまえたちを切るために、わたしの剣がさやから抜き放たれた。その剣は鋭く研ぎすまされ、いなずまのように光っている。 29おまえたちの占い師や偽預言者どもは、おまえたちの神々がバビロンの王の手から救ってくれるから、『安全だ。心配はない』と偽りを言った。こうして、おまえたちを他の悪者とともに死に追いやったのだ。最後の罰の下る日がくるとき、おまえたちは傷ついて死ぬ。 30おまえたちを罰せずに、わたしの剣が元のさやに納められることはない。おまえたちの祖国で滅ぼそう。 31わたしの憤りをぶちまけ、怒りの炎を吹きつけよう。そして、破壊することの上手な、残忍な者どもの手に引き渡そう。 32おまえたちは火に注がれる油で、その血が自分の国で流される。おまえたちは一掃されて、歴史から完全に忘れ去られる。主であるわたしが、こう語ったからだ。」