ሆሴዕ 2 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 2:1-23

1“ወንድሞቻችሁን ‘ሕዝቤ’፣ እኅቶቻችሁንም ‘ተወዳጆቼ’ ብላችሁ ጥሯቸው።

የእስራኤል መቀጣትና መመለስ

2“እናታችሁን ምከሯት፤ ምከሯት፤

እርሷ ሚስቴ አይደለችም፤

እኔም ባሏ አይደለሁምና።

ከፊቷ የዘማዊነት አስተያየትን፣

ከጡቶቿም መካከል ምንዝርናዋን ታስወግድ።

3አለዚያ ገፍፌ ዕርቃኗን አስቀራታለሁ፤

እንደ ተወለደችበትም ቀን አደርጋታለሁ፤

እንደ ምድረ በዳ፣

እንደ ደረቅም ምድር አደርጋታለሁ፤

በውሃ ጥምም እገድላታለሁ።

4ለልጆቿ አልራራላቸውም፤

የምንዝርና ልጆች ናቸውና።

5እናታቸው አመንዝራ ነች፤

በውርደትም ፀንሳቸዋለች፤

እርሷም፣ ‘እንጀራዬንና ውሃዬን ይሰጡኛል፤

ሱፌንና የሐር ልብሴን፣ ዘይቴንና መጠጤን ይሰጡኛል፤

ስለዚህ ውሽሞቼን ተከትዬ እሄዳለሁ’ አለች።

6በዚህ ምክንያት መንገዷን በእሾኽ እዘጋለሁ፤

መውጫ መንገድ እንዳታገኝም ዙሪያዋን በግንብ ዐጥራለሁ።

7ውሽሞቿን ተከትላ ትሄዳለች፤ ነገር ግን አትደርስባቸውም፤

ትፈልጋቸዋለች፤ ሆኖም አታገኛቸውም።

ከዚያም እንዲህ ትላለች፤

‘ወደ ቀድሞ ባሌ እመለሳለሁ፤

የፊተኛው ኑሮዬ ከአሁኑ ይሻለኛልና።’

8እርሷም እህል፣ ዘይትና አዲስ የወይን ጠጅ የሰጠኋት፣

ለበኣል አምልኮ ያደረጉትን፣

ብርንና ወርቅን ያበዛሁላት፣

እኔ እንደ ሆንሁ አላወቀችም።

9“ስለዚህ እህሌን በመከር ጊዜ፣

አዲሱም የወይን ጠጅ በደረሰ ጊዜ እወስዳለሁ፤

ዕርቃኗንም እንዳትሸፍንበት፣

ሱፍና የሐር ልብሴን መልሼ እወስድባታለሁ።

10አሁንም በውሽሞቿ ፊት፣

ነውሯን እገልጣለሁ፤

ከእጄም የሚያድናት የለም።

11የደስታ በዓሎቿን ሁሉ፣

የዓመት በዓሎቿንና፣ የወር መባቻዎቿን

ሰንበቶቿንና የተመረጡ በዓሎቿን ሁሉ አስቀራለሁ።

12ከውሽሞቼ የተቀበልሁት ዋጋ ነው የምትለውን

የወይን ተክሎቿንና የበለስ ዛፎቿን አጠፋለሁ፤

ጫካ አደርገዋለሁ፤

የዱር አራዊትም ይበሉታል።

13ለበኣል አማልክት ዕጣን ስላጠነችባቸው ቀናት

እቀጣታለሁ፤

በጌጣጌጥና በቀለበቶች ራሷን አስጊጣለች፤

ውሽሞቿንም ተከትላ ሄዳለች፤

እኔን ግን ረስታለች”

ይላል እግዚአብሔር

14“ስለዚህ እነሆ፤ አባብላታለሁ፤

ወደ ምድረ በዳም እወስዳታለሁ፤

በፍቅር ቃል አነጋግራታለሁ።

15በዚያም የወይን ተክሏን እመልስላታለሁ፤

የአኮርንም2፥15 አኮር ማለት ችግር ማለት ነው ሸለቆ የተስፋ በር እንዲሆናት አደርጋለሁ።

በዚያም ከግብፅ እንደ ወጣችበት ቀን፣

እንደ ልጅነቷም ጊዜ ትዘምራለች።2፥15 ወይም ትሆናለች

16“በዚያ ቀን፣ ‘ባሌ’ ብለሽ፣

ትጠሪኛለሽ” ይላል እግዚአብሔር

“ከእንግዲህም፣ ‘ጌታዬ’2፥16 ዕብራይስጡ በኣል ይላል ብለሽ አትጠሪኝም።

17የበኣል አማልክትን ስም ከአንደበቷ አስወግዳለሁ፤

ከእንግዲህም ስሞቻቸው አይነሡም።

18በዚያን ቀን ከምድር አራዊትና ከሰማይ ወፎች፣

በምድርም ላይ ከሚንቀሳቀሱ ፍጥረት ጋር፣

ቃል ኪዳን አደርግላቸዋለሁ፤

ሁሉም በሰላም እንዲኖሩ፣

ቀስትን፣ ሰይፍንና ጦርነትን፣

ከምድሪቱ አስወግዳለሁ።

19ለእኔ እንድትሆኚ ለዘላለም ዐጭሻለሁ፤

በጽድቅና በፍትሕ፣

በፍቅርና በርኅራኄም ዐጭሻለሁ።

20በታማኝነት ዐጭሻለሁ፤

አንቺም እግዚአብሔርን ታውቂያለሽ።”

21እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በዚያ ቀን እኔ እመልሳለሁ፤

ለሰማያት እመልሳለሁ፤

እነርሱም ለምድር ምላሽ ይሰጣሉ፤

22ምድርም ለእህል፣

ለአዲስ የወይን ጠጅና ለዘይት ምላሽ ትሰጣለች፤

እነርሱም ለኢይዝራኤል2፥22 ኢይዝራኤል ማለት እግዚአብሔር ይተክላል ማለት ነው ምላሽ ይሰጣሉ።

23ስለ ራሴ ስል በምድሪቱ እተክላታለሁ፤

‘ምሕረትን ያላገኘ’2፥23 ዕብራይስጡ ሎሩሃማ ይላል ብዬ የጠራሁትንም እምረዋለሁ፤

‘ሕዝቤ አይደላችሁም’2፥23 ዕብራይስጡ ሎዓሚ ይላል ተብለው የተጠሩትንም፣ ‘ሕዝቤ’ እላቸዋለሁ፤

እነርሱም፣ ‘አንተ አምላኬ ነህ’ ይላሉ።”

New International Version – UK

Hosea 2:1-23

In Hebrew texts 2:1-23 is numbered 2:3-25. 1‘Say of your brothers, “My people”, and of your sisters, “My loved one”.

Israel punished and restored

2‘Rebuke your mother, rebuke her,

for she is not my wife,

and I am not her husband.

Let her remove the adulterous look from her face

and the unfaithfulness from between her breasts.

3Otherwise I will strip her naked

and make her as bare as on the day she was born;

I will make her like a desert,

turn her into a parched land,

and slay her with thirst.

4I will not show my love to her children,

because they are the children of adultery.

5Their mother has been unfaithful

and has conceived them in disgrace.

She said, “I will go after my lovers,

who give me my food and my water,

my wool and my linen, my olive oil and my drink.”

6Therefore I will block her path with thornbushes;

I will wall her in so that she cannot find her way.

7She will chase after her lovers but not catch them;

she will look for them but not find them.

Then she will say,

“I will go back to my husband as at first,

for then I was better off than now.”

8She has not acknowledged that I was the one

who gave her the grain, the new wine and oil,

who lavished on her the silver and gold –

which they used for Baal.

9‘Therefore I will take away my corn when it ripens,

and my new wine when it is ready.

I will take back my wool and my linen,

intended to cover her naked body.

10So now I will expose her lewdness

before the eyes of her lovers;

no-one will take her out of my hands.

11I will stop all her celebrations:

her yearly festivals, her New Moons,

her Sabbath days – all her appointed festivals.

12I will ruin her vines and her fig-trees,

which she said were her pay from her lovers;

I will make them a thicket,

and wild animals will devour them.

13I will punish her for the days

she burned incense to the Baals;

she decked herself with rings and jewellery,

and went after her lovers,

but me she forgot,’ declares the Lord.

14‘Therefore I am now going to allure her;

I will lead her into the wilderness

and speak tenderly to her.

15There I will give her back her vineyards,

and will make the Valley of Achor2:15 Achor means trouble. a door of hope.

There she will respond2:15 Or sing as in the days of her youth,

as in the day she came up out of Egypt.

16‘In that day,’ declares the Lord,

‘you will call me “my husband”;

you will no longer call me “my master2:16 Hebrew baal”.

17I will remove the names of the Baals from her lips;

no longer will their names be invoked.

18In that day I will make a covenant for them

with the beasts of the field, the birds in the sky

and the creatures that move along the ground.

Bow and sword and battle

I will abolish from the land,

so that all may lie down in safety.

19I will betroth you to me for ever;

I will betroth you in2:19 Or with righteousness and justice,

in2:19 Or with love and compassion.

20I will betroth you in2:20 Or with faithfulness,

and you will acknowledge the Lord.

21‘In that day I will respond,’

declares the Lord

‘I will respond to the skies,

and they will respond to the earth;

22and the earth will respond to the grain,

the new wine and the olive oil,

and they will respond to Jezreel.2:22 Jezreel means God plants.

23I will plant her for myself in the land;

I will show my love to the one I called “Not my loved one2:23 Hebrew Lo-Ruhamah (see 1:6)”.

I will say to those called “Not my people2:23 Hebrew Lo-Ammi (see 1:9)”, “You are my people”;

and they will say, “You are my God.” ’