ዘፍጥረት 1 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 1:1-31

የፍጥረት አጀማመር

1በመጀመሪያ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰማያትንና ምድርን ፈጠረ። 2ምድርም ቅርጽ የለሽና ባዶ ነበረች።1፥2 ወይም ሆነች የምድርን ጥልቅ ስፍራ ሁሉ ጨለማ ውጦት ነበር። የእግዚአብሔርም (ኤሎሂም) መንፈስ በውሆች ላይ ይረብብ ነበር።

3ከዚያም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) “ብርሃን ይሁን” አለ፤ ብርሃንም ሆነ። 4እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ብርሃኑ መልካም እንደ ሆነ አየ፤ ብርሃኑን ከጨለማ ለየ። 5እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ብርሃኑን “ቀን”፣ ጨለማውን “ሌሊት” ብሎ ጠራው። መሸ፤ ነጋም፤ የመጀመሪያ ቀን።

6እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ውሃን ከውሃ የሚለይ ጠፈር በውሆች መካከል ይሁን” አለ። 7ስለዚህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ጠፈርን አድርጎ ከጠፈሩ በላይና ከጠፈሩ በታች ያለውን ውሃ ለየ፤ እንዳለውም ሆነ። 8እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ጠፈርን “ሰማይ” ብሎ ጠራው። መሸ፤ ነጋም፤ ሁለተኛ ቀን።

9ከዚያም እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ከሰማይ በታች ያለው ውሃ በአንድ ስፍራ ይከማች፤ ደረቁ ምድር ይገለጥ” አለ፤ እንዳለውም ሆነ። 10እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ደረቁን ምድር፣ “የብስ”፣ በአንድነት የተሰበሰበውን ውሃ፣ “ባሕር” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ይህ መልካም እንደ ሆነ አየ።

11እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ምድር ዕፀዋትንም፣ እንደየወገናቸው ዘር የሚሰጡ ተክሎችንና በምድር ላይ ዘር ያዘሉ ፍሬ የሚያፈሩ ዛፎችን እንደየወገናቸው ታብቅል” አለ፤ እንዳለውም ሆነ። 12ምድር ዕፀዋትን፣ እንደየወገናቸው ዘር የሚሰጡ ተክሎችንና በውስጣቸው ዘር ያለባቸው ፍሬ የሚያፈሩትን ዛፎች በየወገኑ አበቀለች። እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ይህ መልካም እንደ ሆነ አየ። 13መሸ፤ ነጋም፤ ሦስተኛ ቀን።

14ከዚያም እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ቀኑን ከሌሊት እንዲለዩ፣ የዓመት ወቅቶች፣ ቀናትና ዓመታት የሚጀምሩበትንም እንዲያመለክቱ፣ 15ለምድር ብርሃን የሚሰጡ ልዩ ልዩ ብርሃናት በሰማይ ይሁኑ” አለ፤ እንዳለውም ሆነ። 16እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ ለምድር ብርሃን ይሰጡ ዘንድ ሁለት ታላላቅ ብርሃናት አደረገ፤ ታላቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፣ ታናሹ ብርሃን በሌሊት እንዲሠለጥን አደረገ። እንዲሁም ከዋክብትን አደረገ። 17ለምድር ብርሃን እንዲሰጡ እነዚህን በሰማይ ጠፈር አኖራቸው። 18ይኸውም በቀንና በሌሊት እንዲሠለጥኑ፣ ብርሃንን ከጨለማ እንዲለዩ ነው። እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ይህ መልካም እንደ ሆነ አየ። 19መሸ፤ ነጋም፣ አራተኛ ቀን።

20እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ውሆች ሕይወት ባላቸው በሕያዋን ፍጡራን ይሞሉ፤ ወፎች ከምድር በላይ በሰማይ ጠፈር ይብረሩ” አለ። 21በዚህ መሠረት፣ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) በባሕር ውስጥ የሚኖሩ ታላላቅ ፍጡራንን፣ በውሃ ውስጥ የሚርመሰመሱ ሕይወት ያላቸውን ነገሮች ሁሉ እንደየወገናቸው እንዲሁም ክንፍ ያላቸውን ወፎች ሁሉ እንደየወገናቸው ፈጠረ፤ እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ይህ መልካም እንደ ሆነ አየ። 22እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “ብዙ ተባዙ፤ የባሕርንም ውሃ ሙሏት፤ ወፎችም በምድር ላይ ይብዙ” ብሎ ባረካቸው። 23መሸ፤ ነጋም፤ አምስተኛ ቀን።

24እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ምድር ሕያዋን ፍጡራንን እንደየወገናቸው፣ ከብቶችን፣ በምድር ላይ የሚሳቡ ፍጡራንንና የዱር እንስሳትን እያንዳንዱን እንደ ወገኑ ታስገኝ” አለ፤ እንዳለውም ሆነ። 25እግዚአብሔር (ኤሎሂም) የዱር እንስሳትን እንደየወገናቸው፣ ከብቶችን እንደየወገናቸው፣ እንዲሁም በምድር ላይ የሚሳቡ ፍጡራንን እንደየወገናቸው አደረገ። እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ይህ መልካም እንደ ሆነ አየ።

26እግዚአብሔር (ኤሎሂም)፣ “ሰውን በመልካችን፣ በአምሳላችን እንሥራ፤ በባሕር ዓሦች፣ በሰማይ ወፎች፣ በከብቶች፣ በምድር1፥26 ዕብራይስጡም እንደዚሁ ሲሆን ሱርስቱ ግን የዱር እንስሳት ሁሉ ይለዋል። ሁሉ ላይ፣ እንዲሁም በምድር በሚሳቡ ፍጡራን ሁሉ ላይ ሥልጣን ይኑራቸው” አለ።

27ስለዚህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰውን በራሱ መልክ ፈጠረው፤

በእግዚአብሔር (ኤሎሂም) መልክ ፈጠረው፤

ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው።

28እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “ብዙ ተባዙ፤ ምድርን ሙሏት፤ ግዟትም፤ የባሕርን ዓሦች፣ የሰማይን ወፎች፣ እንዲሁም በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትን ሕያዋን ፍጡራንን ሁሉ ግዟቸው” ብሎ ባረካቸው።

29እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) እንዲህ አለ፤ “በምድር ላይ ያሉትን ዘር የሚሰጡ ተክሎችን ሁሉ፣ በፍሬያቸው ውስጥ ዘር ያለባቸውን ዛፎች ሁሉ ምግብ ይሆኑላችሁ ዘንድ ሰጥቻችኋለሁ። 30እንዲሁም ለምድር አራዊት ሁሉ፣ ለሰማይ ወፎች ሁሉ፣ በምድር ላይ ለሚንቀሳቀሱ ሕያዋን ፍጡራን ሁሉ ማንኛውም ለምለም ተክል ምግብ እንዲሆናቸው ሰጥቻለሁ” እንዳለውም ሆነ።

31እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ያደረገውን ሁሉ አየ፤ እነሆም፣ እጅግ መልካም ነበረ። መሸ፤ ነጋም፤ ስድስተኛ ቀን።

Persian Contemporary Bible

پيدايش 1:1-31

داستان آفرينش

1در آغاز، هنگامی كه خدا آسمانها و زمين را آفريد، 2زمين، خالی و بی‌شكل بود، و روح خدا روی توده‌های تاريکِ بخار حركت می‌كرد. 3خدا فرمود: «روشنايی بشود.» و روشنايی شد. 4خدا روشنايی را پسنديد و آن را از تاريكی جدا ساخت. 5او روشنايی را «روز» و تاريكی را «شب» ناميد. شب گذشت و صبح شد. اين، روز اول بود.

6سپس خدا فرمود: «توده‌های بخار از هم جدا شوند تا آسمان در بالا و اقيانوسها در پايين تشكيل گردند.» 7‏-8خدا توده‌های بخار را از آبهای پايين جدا كرد و آسمان را به وجود آورد. شب گذشت و صبح شد. اين، روز دوم بود.

9‏-10پس از آن خدا فرمود: «آبهای زير آسمان در يكجا جمع شوند تا خشكی پديد آيد.» و چنين شد. خدا خشكی را «زمين» و اجتماع آبها را «دريا» ناميد و خدا اين را پسنديد. 11‏-12سپس خدا فرمود: «انواع نباتات و گياهان دانه‌دار و درختان ميوه‌دار در زمين برويند و هر يک، نوع خود را توليد كنند.» همينطور شد و خدا خشنود گرديد. 13شب گذشت و صبح شد. اين، روز سوم بود.

14‏-15سپس خدا فرمود: «در آسمان اجسام درخشانی باشند تا زمين را روشن كنند و روز را از شب جدا نمايند و روزها، فصلها و سالها را پديد آورند.» و چنين شد. 16پس خدا دو روشنايی بزرگ ساخت تا بر زمين بتابند: روشنايی بزرگتر برای حكومت بر روز و روشنايی كوچكتر برای حكومت بر شب. او همچنين ستارگان را ساخت. 17خدا آنها را در آسمان قرار داد تا زمين را روشن سازند، 18بر روز و شب حكومت كنند، و روشنايی و تاريكی را از هم جدا نمايند. و خدا خشنود شد. 19شب گذشت و صبح شد. اين، روز چهارم بود.

20سپس خدا فرمود: «آبها از موجودات زنده پر شوند و پرندگان بر فراز آسمان به پرواز درآيند.» 21‏-22پس خدا حيوانات بزرگ دريايی و انواع جانوران آبزی و انواع پرندگان را آفريد. خدا از اين نيز خشنود شد و آنها را بركت داده، فرمود: «موجودات دريايی بارور و زياد شوند و آبها را پُر سازند و پرندگان نيز روی زمين زياد شوند.» 23شب گذشت و صبح شد. اين، روز پنجم بود.

24سپس خدا فرمود: «زمين، انواع جانوران و حيوانات اهلی و وحشی و خزندگان را به وجود آوَرَد.» و چنين شد. 25خدا انواع حيوانات اهلی و وحشی و تمام خزندگان را به وجود آورد، و از كار خود خشنود گرديد.

26سرانجام خدا فرمود: «انسان را شبيه خود بسازيم، تا بر حيوانات زمين و ماهيان دريا و پرندگان آسمان فرمانروايی كند.» 27پس خدا انسان را شبيه خود آفريد. او انسان را زن و مرد خلق كرد 28و ايشان را بركت داده، فرمود: «بارور و زياد شويد، زمين را پُر سازيد، بر آن تسلط يابيد، و بر ماهيان دريا و پرندگان آسمان و همهٔ حيوانات فرمانروايی كنيد. 29تمام گياهان دانه‌دار و ميوه‌های درختان را برای خوراک به شما دادم، 30و همهٔ علفهای سبز را به حيوانات و پرندگان و خزندگان بخشيدم.»

31آنگاه خدا به آنچه آفريده بود نظر كرد و كار آفرينش را از هر لحاظ عالی ديد. شب گذشت و صبح شد. اين، روز ششم بود.