ዘካርያስ 5 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 5:1-11

በራሪው የመጽሐፍ ጥቅልል

1እንደ ገናም ተመለከትሁ፤ በዚያም በፊቴ በራሪ የመጽሐፍ ጥቅልል አየሁ።

2እርሱም፣ “ምን ታያለህ?” ሲል ጠየቀኝ። እኔም፣ “ርዝመቱ ሃያ ክንድ፣ ወርዱ5፥2 ዕብራይስጡ፣ ርዝመቱ ሃያ ክንድ፣ ወርዱ 10 ክንድ ወይም ርዝማኔው ዘጠኝ ሜትር፣ ስፋቱ አራት ተኩል ሜትር ይሆናል። ዐሥር ክንድ የሆነ በራሪ የመጽሐፍ ጥቅልል አያለሁ” አልሁት። 3እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “ይህ በምድር ሁሉ ላይ የሚወጣ ርግማን ነው፤ በአንደኛው በኩል እንደ ተጻፈው የሚሰርቅ ሁሉ ይጠፋል፤ በሌላው በኩል ደግሞ እንደ ተጻፈው በሐሰት የሚምል ሁሉ ይጠፋልና። 4እግዚአብሔር ጸባኦት ‘እኔ ርግማኑን አመጣዋለሁ፤ እርሱም ወደ ሌባው ቤትና በስሜ በሐሰት ወደሚምለው ሰው ቤት ይገባል፤ በዚያም ይቀመጣል፤ ቤቱን፣ ዕንጨቱንና ድንጋዩን ያጠፋል’ ይላል።”

በቅርጫት ውስጥ ያለች ሴት

5ከዚያም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ ወደ እኔ መጥቶ፣ “ወደ ላይ ተመልከት፤ ይህ የሚመጣው ምን እንደ ሆነ እይ” አለኝ።

6እኔም፣ “ምንድን ነው?” አልሁት። እርሱም፣ “የኢፍ መስፈሪያ5፥6 ከ7-11 ካለው ጭምር፣ የእህል መስፈሪያ ወይም ቍና ማለት ነው። ነው” አለኝ። ቀጥሎም “ይህ በምድሪቱ ሁሉ ላይ ያለው የሕዝቡ በደል5፥6 ወይም መምሰል ማለት ሊሆን ይችላል። ነው” አለኝ።

7ከዚያም ከእርሳስ የተሠራው ክዳን ተነሣ፤ የኢፍ መስፈሪያ ውስጥ አንዲት ሴት ተቀምጣ ነበር። 8እርሱም፣ “ይህች ርኩሰት ናት” ብሎ ወደ ኢፍ መስፈሪያ መልሶ አስገባት፤ የእርሳሱንም ክዳን ወደ ቅርጫቱ አፍ ገፍቶ ገጠመው።

9ከዚያም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ እነሆም፣ ከፊቴ ሁለት ሴቶች ነበሩ፤ በክንፎቻቸውም ነፋስ ነበር፤ ክንፎቻቸውም እንደ ሽመላ ክንፎች ነበሩ፤ የኢፍ መስፈሪያውንም በምድርና በሰማይ መካከል አነሡት።

10ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውንም መልአክ፣ “ቅርጫቱን የሚወስዱት ወዴት ነው?” አልሁት።

11እርሱም፣ “ቤት ሊሠሩለት ወደ ባቢሎን5፥11 ዕብራይስጡ ሺናር ይለዋል። ምድር ይወስዱታል፤ በተዘጋጀም ጊዜ ወስደው በቦታው ያስቀምጡታል” አለኝ።

Bibelen på hverdagsdansk

Zakariasʼ Bog 5:1-11

Den flyvende bogrulle

1I det næste syn så jeg en bogrulle, der kom flyvende gennem luften. 2„Hvad ser du?” spurgte englen. „En flyvende bogrulle!” svarede jeg. „Den ser ud til at være omkring 10 m lang og 5 m høj.”

3„På den bogrulle har Herren skrevet en dom, som gælder alle i hele landet,” forklarede englen. „De, som stjæler og lyver, har længe nok undgået deres straf. 4Men nu sender jeg min dom over enhver, der stjæler, og over alle, der sværger falsk ved mit navn, siger Herren. Dommen vil ramme deres hjem og familier og ødelægge dem totalt.”

Kvinden i tønden

5Derefter kom englen igen hen til mig. „Kig op! Kan du se noget, der kommer svævende herhen?” spurgte han. 6„Ja, hvad er det?” spurgte jeg. „En tønde til at måle korn med, men den er fyldt med landets synder,” forklarede han.

7I det samme blev tøndens tunge blylåg løftet, og jeg så, at der sad en kvinde nede i den. 8„Den kvinde symboliserer ondskaben på jorden,” forklarede englen. Så skubbede han hende tilbage i tønden og lagde låget på.

9Da jeg kiggede op igen, så jeg to kvinder med storkevinger komme svævende gennem luften. De løftede tønden op og fløj af sted med den. 10„Hvor bærer de tønden hen?” spurgte jeg englen.

11„Til Babylon,” svarede han. „Der vil man bygge et tempel for kvinden, og når det er færdigt, vil man anbringe hende på en piedestal.”