ካህናቱ አገልግሎታቸውን ጀመሩ
1በስምንተኛውም ቀን ሙሴ አሮንንና ልጆቹን እንዲሁም የእስራኤልን ሽማግሌዎች ጠራቸው። 2አሮንንም እንዲህ አለው፤ “የኀጢአት መሥዋዕት እንዲሆንልህ አንድ እንቦሳ እንዲሁም የሚቃጠል መሥዋዕት እንዲሆንልህ አንድ አውራ በግ ወስደህ፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አቅርባቸው፤ ሁለቱም እንከን የሌለባቸው ይሁኑ። 3እስራኤላውያንንም እንዲህ በላቸው፤ ‘ለኀጢአት መሥዋዕት አንድ አውራ ፍየል፣ ለሚቃጠል መሥዋዕት እንከን የሌለባቸውን የአንድ ዓመት እንቦሳና የአንድ ዓመት ጠቦት፣ 4ለኅብረት መሥዋዕት9፥4 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል፤ እንዲሁም 18፥22 ይመ። አንድ በሬና9፥4 የዕብራይስጥ ቃል ተባዕትና እንስትን ሊያጠቃልል ይችላል፤ እንዲሁም 18፡19 ይመ አንድ አውራ በግ በዘይት ከተለወሰ የእህል ቍርባን ጋር በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ለመሠዋት አቅርቡ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ዛሬ ይገለጥላችኋልና።’ ”
5እነርሱም ሙሴ ያዘዛቸውን ሁሉ ወደ መገናኛው ድንኳን ደጃፍ አመጡ፤ ሕዝቡም በሙሉ ቀርበው በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ቆሙ። 6ሙሴም፣ “የእግዚአብሔር (ያህዌ) ክብር ይገለጥላችሁ ዘንድ፣ እንድታደርጉት እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዛችሁ ይህ ነው” አለ።
7ሙሴ አሮንን፣ “ወደ መሠዊያው ቀርበህ የኀጢአት መሥዋዕትህንና የሚቃጠለውን መሥዋዕትህን ሠዋ፤ ለራስህና ለሕዝቡም አስተስርይ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት የሕዝቡን መሥዋዕት አቅርብ፤ አስተስርይላቸውም” አለው።
8አሮንም ወደ መሠዊያው መጥቶ ስለ ራሱ የኀጢአት መሥዋዕት የቀረበውን እንቦሳ ዐረደው። 9ልጆቹም ደሙን አመጡለት፤ እርሱም ጣቱን በደሙ ውስጥ ነክሮ የመሠዊያውን ቀንዶች ቀባ፤ የተረፈውንም ደም በመሠዊያው ግርጌ አፈሰሰው። 10እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት የኀጢአት መሥዋዕቱን ሥብ፣ ኵላሊቶቹንና የጕበቱን ሽፋን በመሠዊያው ላይ አቃጠለው፤ 11ሥጋውንና ቍርበቱንም ከሰፈሩ ውጭ በእሳት አቃጠለው።
12ከዚህ በኋላ አሮን የሚቃጠለውን መሥዋዕት ዐረደ፤ ልጆቹ ደሙን አቀበሉት፤ እርሱም ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ረጨ። 13ልጆቹም የሚቃጠለውን መሥዋዕት ብልት አንድ በአንድ፣ ጭንቅላቱን ሳይቀር አምጥተው ሰጡት፤ እርሱም በመሠዊያው ላይ አቃጠለው። 14የሆድ ዕቃውንና እግሮቹን ዐጥቦ በመሠዊያው ላይ ካለው ከሚቃጠለው መሥዋዕት በላይ አቃጠለ። 15አሮንም የሕዝቡን መሥዋዕት አቀረበ፤ ስለ ሕዝቡ የኀጢአት መሥዋዕት የሆነውን ፍየል ወስዶ ዐረደው፤ እንደ ፊተኛው ሁሉ ይህንም በኀጢአት መሥዋዕትነት ሠዋው።
16የሚቃጠለውንም መሥዋዕት አምጥቶ በሥርዐቱ መሠረት አቀረበው። 17የእህል ቍርባኑን አመጣ፤ ከላዩም ዕፍኝ ሙሉ ወስዶ ጧት ጧት ከሚቀርበው የሚቃጠል መሥዋዕት በተጨማሪ በመሠዊያው ላይ አቃጠለ።
18አሮንም ስለ ሕዝቡ የኅብረት መሥዋዕት የቀረቡትን በሬውንና አውራ በጉን ዐረደ፤ ልጆቹም ደሙን አመጡለት፤ እርሱም ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ረጨ። 19የበሬውንና የአውራ በጉን ሥብ፦ ላቱን፣ የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ፤ ኵላሊቶቹንና የጕበቱን ሽፋን፣ 20በፍርምባዎቹ ላይ አስቀመጡ፤ አሮንም ሥቡን በመሠዊያው ላይ አቃጠለ፤ 21ፍርምባዎቹንና የቀኝ ወርቹንም ሙሴ ባዘዘው መሠረት፣ የመወዝወዝ መሥዋዕት አድርጎ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወዘወዘው።
22አሮንም እጆቹን ወደ ሕዝቡ ዘርግቶ ባረካቸው፤ የኀጢአት መሥዋዕቱን፣ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረቱን መሥዋዕት ካቀረበ በኋላ ወረደ።
23ከዚህ በኋላ፣ ሙሴና አሮን ወደ መገናኛው ድንኳን ገቡ፤ ከዚያ ሲወጡም ሕዝቡን ባረኩ፤ የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ለሕዝቡ ሁሉ ተገለጠ። 24እሳት ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ዘንድ ወጥቶ፣ በመሠዊያው ላይ የነበረውን በላ፤ ሕዝቡም ሁሉ ይህን ባዩ ጊዜ እልል አሉ፤ በግንባራቸውም ተደፉ።
亚伦献祭
1第八天,摩西召来亚伦父子们和以色列的众长老。 2他对亚伦说:“你要在耶和华面前献上一头公牛犊作赎罪祭、一只公绵羊作燔祭,这些祭牲都要毫无残疾。 3然后,你要告诉以色列人,‘你们要取一只公山羊作赎罪祭、毫无残疾的一岁牛犊和羊羔各一只作燔祭、 4公牛和公绵羊各一只作平安祭,连同调油的素祭一起献给耶和华,因为今天耶和华要向你们显现。’” 5于是,以色列人遵照摩西的吩咐,把祭物带到会幕前。全体会众都聚集到那里,站在耶和华面前。 6摩西对他们说:“耶和华吩咐你们这样做,是为了向你们显出祂的荣耀。” 7随后,摩西对亚伦说:“你要到坛前来,献上你的赎罪祭和燔祭,为自己和民众赎罪。也要按照耶和华的吩咐,为百姓献上他们的祭物,为他们赎罪。”
8于是,亚伦走到坛前,宰杀为他作赎罪祭的牛犊。 9他儿子们把牛犊的血递给他,他用手指蘸血抹在坛角上,将剩下的血倒在坛脚旁。 10他照耶和华对摩西的吩咐,在坛上焚烧牛犊的脂肪、肾脏和肝叶, 11把皮和肉带到营外焚烧。
12亚伦宰了燔祭祭牲,他儿子们把祭牲的血递给他洒在祭坛四周。 13他们将祭牲切成块,连头颅一起交给亚伦献在坛上焚烧。 14亚伦洗净祭牲的内脏和腿,放在祭坛的燔祭上焚烧。
15随后,亚伦为民众献祭。他牵来那只为民众作赎罪祭的公山羊,宰杀后,像刚才为自己献赎罪祭一样为他们献上赎罪祭。 16他又牵来燔祭祭牲,依照条例献上燔祭。 17除了早晨的燔祭,亚伦又取来素祭,从中拿了一把献在坛上焚烧。 18然后,他宰了公牛和公绵羊,为民众献平安祭。他儿子们把祭牲的血递给他,他把血洒在祭坛四周。 19他们把公牛和公绵羊的脂肪,即肥尾巴、遮盖内脏的脂肪、肾脏和肝叶, 20放在祭牲的胸上,然后亚伦把那些脂肪放在坛上焚烧, 21将胸肉和右腿肉作为摇祭在耶和华面前摇一摇,都遵照摩西的吩咐。
22亚伦献完赎罪祭、燔祭和平安祭,举手为民众祝福后,走下祭坛。 23之后,摩西和亚伦走进会幕,又出来为民众祝福。这时,耶和华的荣耀向所有民众显现。 24有火从耶和华那里降下来,烧尽祭坛上的燔祭和脂肪。民众看见这景象,都欢呼起来,俯伏在地。