አሮንና ልጆቹ ካህናት ሆነው መሾማቸው
8፥1-36 ተጓ ምብ – ዘፀ 29፥1-37
1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“አሮንንና ልጆቹን፣ ልብሰ ተክህኖውን፣ የመቅቢያ ዘይቱን፣ ለኀጢአት መሥዋዕት የሚሆነውን ወይፈን፣ ሁለቱን አውራ በጎችና እርሾ ሳይገባበት የተጋገረው ቂጣ ያለበትን መሶብ አምጣ፤ 3ማኅበሩን በሙሉ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ሰብስብ።” 4ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው አደረገ፤ ማኅበሩም በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ተሰበሰበ።
5ሙሴም ማኅበሩን፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲደረግ ያዘዘው ይህ ነው” አላቸው። 6ሙሴም አሮንንና ልጆቹን ወደ ፊት አወጣቸው፤ በውሃም ዕጠባቸው። 7አሮንን እጀ ጠባብ አለበሰው፤ መቀነት አስታጠቀው፤ ቀሚስ አጠለቀለት፤ ኤፉድ ደረበለት፤ በልዩ ጥበብ በተጠለፈው መታጠቂያ ኤፉዱን አስታጠቀው፤ በላዩም አሰረው፤ 8የደረት ኪሱን በላዩ አደረገለት፤ በደረት ኪሱም ውስጥ ኡሪምንና ቱሚምን አኖረ። 9እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘውም መሠረት፣ ሙሴ ጥምጥሙን በአሮን ራስ ላይ አደረገ፤ በጥምጥሙም ላይ በፊት ለፊቱ በኩል የተቀደሰውን የወርቅ አክሊል አደረገለት።
10ሙሴም መቅቢያ ዘይቱን ወሰደ፤ ማደሪያ ድንኳኑንና በውስጡ የሚገኘውን ሁሉ ቀብቶ ቀደሰ። 11ከዘይቱም ጥቂት ወስዶ በመሠዊያው ላይ ሰባት ጊዜ ረጨ፤ ይቀድሳቸውም ዘንድ መሠዊያውን ከነመገልገያ ዕቃው ሁሉ እንዲሁም የመታጠቢያ ሳሕኑን ከነማስቀመጫው በዘይት ቀባ። 12ከመቅቢያ ዘይቱም በአሮን ራስ ላይ አፈሰሰ፤ የተቀደሰ እንዲሆንም ቀባው። 13እግዚአብሔርም (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት ሙሴ፣ የአሮንን ልጆች ወደ ፊት አቅርቦ እጀ ጠባብ አለበሳቸው፤ መታጠቂያ አስታጠቃቸው፤ ቆብም ደፋላቸው።
14ሙሴም የኀጢአት መሥዋዕት የሆነውን ወይፈን አመጣ፤ አሮንና ልጆቹም በወይፈኑ ራስ ላይ እጃቸውን ጫኑ። 15ሙሴም ወይፈኑን ዐረደ፤ ደሙንም ወስዶ መሠዊያውን ያነጻ ዘንድ በጣቱ የመሠዊያውን ቀንዶች ሁሉ ቀባ፤ የቀረውንም ደም በመሠዊያው ሥር አፈሰሰው። ለመሠዊያውም እንዲህ አድርጎ ያስተሰርይለት ዘንድ ቀደሰው። 16ሙሴም የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሁሉ፣ የጕበቱን ሽፋን፣ ኵላሊቶችንና ሥባቸውን ወስዶ በመሠዊያው ላይ አቃጠለ። 17ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት ወይፈኑን፣ ቈዳውን፣ ሥጋውንና ፈርሱን ከሰፈር ውጭ አቃጠለ።
18ሙሴ ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚሆነውን አውራ በግ አቀረበ፤ አሮንና ልጆቹም እጃቸውን በበጉ ላይ ጫኑ። 19ሙሴም በጉን ዐርዶ ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ረጨ። 20በጉንም በየብልቱ ቈራረጠ፤ ጭንቅላቱን፣ ብልቶቹንና ሥቡን አቃጠለ። 21ሆድ ዕቃውንና እግሮቹን በውሃ አጠበ፤ ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት፣ በጉን በሙሉ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም ደስ የሚያሰኝ የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ በመሠዊያው ላይ አቃጠለው።
22ሙሴ ለቅድስና የሚሆነውን ሌላ አውራ በግ አቀረበ፤ አሮንና ልጆቹም እጆቻቸውን በበጉ ራስ ላይ ጫኑ። 23ሙሴ አውራ በጉን ዐረደ፤ ከደሙም ጥቂት ወስዶ የአሮንን ቀኝ ጆሮ ጫፍ፣ የቀኝ እጁን አውራ ጣትና የቀኝ እግሩን አውራ ጣት አስነካ፤ 24የአሮንንም ልጆች ወደ ፊት ጠራ፤ ከደሙም ጥቂት ወስዶ የቀኝ ጆሯቸውን ጫፍ፣ የቀኝ እጃቸውን አውራ ጣትና የቀኝ እግራቸውን አውራ ጣት አስነካ፤ የቀረውንም ደም በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ረጨ። 25ሥቡን፣ ላቱን፣ ሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ ሁሉ፣ የጕበቱን ሽፋን፣ ሁለቱን ኵላሊቶችና ሥባቸውን እንዲሁም ቀኝ ወርቹን ወሰደ፤ 26በእግዚአብሔርም (ያህዌ) ፊት ካለው፣ ያለ እርሾ የተጋገረ ዳቦ ካለበት መሶብ ላይ አንድ ኅብስት፣ አንድ በዘይት የተጋገረ ዳቦ እንዲሁም ስስ ቂጣ ወስዶ በሥቦቹና በቀኝ ወርቹ ላይ አኖረ። 27እነዚህንም ሁሉ ለአሮንና ለልጆቹ በእጃቸው ሰጣቸው፤ እነርሱም የሚወዘወዝ መሥዋዕት አድርገው በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወዘወዙት። 28ሙሴም ከእጃቸው ተቀብሎ፣ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርጎ በመሠዊያው ላይ በሚቃጠለው መሥዋዕት ላይ አቃጠለው። 29ሙሴም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት፣ ድርሻው የሆነውን ክህነት የመስጫውን አውራ በግ ፍርምባ ወስዶ የሚወዘወዝ መሥዋዕት በማድረግ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወዘወዘው።
30ቀጥሎም ሙሴ በመቅቢያው ዘይትና በመሠዊያው ላይ ካለው ደም ጥቂት ወስዶ፣ በአሮንና በልብሱ እንዲሁም በአሮን ልጆችና በልብሳቸው ላይ ረጨ፤ በዚህም ሁኔታ አሮንንና ልብሱን፣ ልጆቹንና ልብሳቸውን ቀደሰ።
31ሙሴም አሮንና ልጆቹን እንዲህ አላቸው፤ “ሥጋውን በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ቀቅሉት፤ በዚያም፣ ‘አሮንና ልጆቹ ይብሉት’ ተብዬ በታዘዝሁት8፥31 ወይም ብዬ ባዘዝሁት መሠረት፣ በክህነት መስጫው መሥዋዕት መሶብ ውስጥ ካለው ኅብስት ጋር ብሉት፤ 32የተረፈውንም ሥጋና ኅብስት በእሳት አቃጥሉ። 33የክህነት መቀበያችሁ ሥርዐት እስከሚፈጸምበት እስከ ሰባት ቀን ድረስ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ቈዩ፤ ሥርዐቱንም ለመፈጸም ሰባት ቀን ይወስዳልና። 34ዛሬ የተፈጸመው ይህ ሥርዐት ለእናንተ ማስተስረያ እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ነው። 35እንዳትሞቱ ሰባቱን ቀንና ሌሊት ከመገናኛው ድንኳን ደጃፍ አትለዩ፤ የእግዚአብሔርንም (ያህዌ) ሥርዐት ጠብቁ፤ የታዘዝሁት እንዲህ ነውና።” 36አሮንና ልጆቹም እግዚአብሔር (ያህዌ) በሙሴ አማካይነት ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ።
膏立亚伦父子们做祭司
1耶和华对摩西说: 2“你把亚伦父子们带来,也要带圣衣、膏油、一头作赎罪祭的公牛、两只公绵羊和一篮无酵饼, 3然后把全体会众招聚到会幕门前。” 4摩西按照耶和华的指示行事,会众都聚集在会幕门前。
5摩西告诉会众:“这是耶和华吩咐我做的事。” 6他把亚伦父子们带来,用水洗他们。 7摩西给亚伦穿上内袍,束上腰带,穿上外袍,套上以弗得,用精巧的带子把以弗得系在亚伦身上, 8然后给他戴上胸牌,把乌陵和土明放在胸牌内, 9再把礼冠戴在他头上,在礼冠前系上金牌,即圣冠,都遵照耶和华的吩咐。
10摩西拿膏油抹圣幕和圣幕里的一切物件,使它们圣洁; 11再用膏油在祭坛上洒七次,又抹祭坛和祭坛上的器具、洗濯盆和盆座,使它们圣洁。 12然后,摩西把膏油倒在亚伦头上膏立他,使他圣洁。 13摩西又把亚伦的儿子们带来,给他们穿上内袍,束上腰带,裹上头巾,都遵照耶和华的吩咐。
14摩西牵来那头作赎罪祭的公牛,亚伦父子们把手放在牛头上。 15摩西宰了牛,用手指蘸一些牛血抹在祭坛的四角上,以洁净祭坛;把剩下的血倒在祭坛脚旁,使祭坛圣洁。 16他取出遮盖内脏的脂肪、肝叶、两个肾脏和肾脏上的脂肪,放在坛上焚烧, 17又照耶和华的吩咐,把公牛的皮、肉和粪便带到营外烧掉。
18然后,摩西献上作燔祭的公绵羊,亚伦父子们把手放在羊头上。 19摩西宰了那只羊,将羊血洒在祭坛周围; 20把羊切成块,焚烧羊头、肉块和脂肪; 21用水洗净羊的内脏和腿,放在坛上焚烧,作蒙耶和华悦纳的馨香火祭,都遵照耶和华的吩咐。
22摩西献上另一只为授圣职而献的公绵羊。亚伦父子们把手放在羊头上。 23摩西宰了羊,将一些羊血抹在亚伦的右耳垂、右手大拇指和右脚大脚趾上。 24他又把亚伦的儿子们带来,将一些血抹在他们的右耳垂、右手大拇指和右脚大脚趾上,然后把剩下的血都洒在祭坛四周。 25他取下羊的右腿和脂肪,即肥尾巴、遮盖内脏的脂肪、肝叶、两个肾脏和肾脏上的脂肪, 26又从放在耶和华面前盛无酵饼的篮子中取一个无酵饼、一个油饼和一个薄饼,放在羊的右腿和脂肪上。 27他把这些放在亚伦父子们的手上,作为摇祭在耶和华面前摇一摇。 28随后,他从他们手上拿过这些祭物,放在祭坛的燔祭上焚烧,作为授圣职时献的祭。这是蒙耶和华悦纳的馨香火祭。 29摩西又把祭牲的胸肉作为摇祭在耶和华面前摇一摇,这是他授圣职时所应得之份,都遵照耶和华的吩咐。
30摩西拿了一些膏油和坛上的血,洒在亚伦和他的衣服上,也洒在他儿子们和他们的衣服上,使亚伦父子们和他们的衣服圣洁。
31摩西对亚伦父子们说:“你们要照我的指示在会幕门口煮祭肉吃,也要吃篮子里为授圣职而献的饼。 32吃剩的肉和饼,你们要烧掉。 33你们的圣职礼为期七天,这七天之内,你们不可走出会幕门口。 34今天所做的这一切都是耶和华吩咐的,是为你们赎罪。 35七天之内,你们必须日夜待在会幕门口,要遵守耶和华的吩咐,免得你们死亡。这是耶和华对我的吩咐。” 36于是,亚伦父子们遵行了耶和华借摩西吩咐的一切。