1“ ‘አንድ ሰው ስላየውና ስለሚያውቀው ነገር ሕጋዊ ምስክርነቱን እንዲሰጥ ተጠይቆ ቃሉን ለመስጠት ፈቃደኛ ባይሆን፣ ይህ ሰው ኀጢአት ሠርቷልና ይጠየቅበታል።
2“ ‘ማንኛውም ሰው ሳያውቅ በሥርዐቱ መሠረት የተከለከለውን ርኩስ ነገር ቢነካ፣ ይኸውም፦ የረከሰ የአውሬ በድን ወይም የረከሰ የቤት እንስሳ በድን ወይም በደረቱ እየተሳበ የሚንቀሳቀሰውን የረከሰ ፍጥረት በድን ቢነካ ይህ ሰው ረክሷል፤ በደለኛም ነው።
3“ ‘ወይም የሰውን ርኩሰት ይኸውም ርኩስ የሚያደርገውን ማናቸውንም ነገር ሳያውቅ ቢነካ፣ ነገሩን ባወቀ ጊዜ በደለኛ ይሆናል።
4“ ‘ሰዎች በሚምሉበት በማናቸውም ነገር፣ በጎ ወይም ክፉ ለማድረግ ሳያስብ በግዴለሽነት ቢምል በኋላ ግን ነገሩን ባወቀ ጊዜ በደለኛ ይሆናል።
5“ ‘ማንኛውም ሰው ከእነዚህ በአንዱ በደለኛ ሆኖ ቢገኝ፣ የትኛውን ኀጢአት እንደ ሠራ ገልጾ መናዘዝ አለበት፤ 6ስለ ኀጢአቱም ቅጣት የኀጢአት መሥዋዕት እንድትሆነው ከመንጋው አንዲት የበግ ወይም የፍየል እንስት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ያቅርብ፤ ካህኑም ስለ ኀጢአቱ ያስተሰርይለታል።
7“ ‘ሰውየው ስለ ሠራው ኀጢአት በግ ለማቅረብ ዐቅሙ ካልፈቀደ ሁለት ዋኖሶች ወይም ሁለት የዋኖስ ጫጩቶች የመጀመሪያውን ለኀጢአት መሥዋዕት፣ ሁለተኛውን ለሚቃጠል መሥዋዕት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ያቅርብ። 8ወደ ካህኑም ያምጣቸው፤ እርሱም ለኀጢአት መሥዋዕት የምትሆነውን አስቀድሞ ያቅርብ፤ ራሷን ዐንገቷ ላይ ይቈልምም፤ ነገር ግን ቈርጦ አይጣል፤ 9ከኀጢአት መሥዋዕቱም ጥቂት ደም ወስዶ በመሠዊያው ዙሪያ ላይ ይርጨው፤ የተረፈውም ደም ሁሉ በመሠዊያው ግርጌ ይፍሰስ፤ ይህም የኀጢአት መሥዋዕት ነው። 10ካህኑም ቀደም ሲል በታዘዘው መሠረት ሁለተኛዋን የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ ያቅርብ፤ ካህኑም የሰውየውን ኀጢአት ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል።
11“ ‘ሰውየው ሁለት ርግቦች ወይም ሁለት የዋኖስ ጫጩቶች ለማቅረብ ዐቅሙ ካልፈቀደ፣ ስለ ሠራው ኀጢአት የኢፍ መስፈሪያ5፥11 ሁለት ሊትር ገደማ ይሆናል አንድ ዐሥረኛ የላመ ዱቄት ለኀጢአት መሥዋዕት ያቅርብ፤ ነገር ግን የኀጢአት መሥዋዕት ስለሆነ ዘይት አያፍስስበት፤ ዕጣንም አይጨምርበት፤ 12ከዚያም ለካህኑ ያቅርብ፤ ካህኑም ለመታሰቢያ እንዲሆን ዕፍኝ ሙሉ ይዝገንለት፤ በእሳት ከሚቀርበውም ቍርባን በላይ አድርጎ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በመሠዊያው ላይ በእሳት ያቃጥለው፤ ይህም የኀጢአት መሥዋዕት ነው። 13ሰውየው ከእነዚህ በአንዱ ኀጢአት ቢሠራ፣ ካህኑ በዚህ ሁኔታ ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል። ከመሥዋዕቱ የተረፈውም እንደ እህል ቍርባን ሁሉ ለካህኑ ይሆናል።’ ”
የበደል መሥዋዕት
14እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 15“ማንኛውም ሰው በደል ቢፈጽም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ከተቀደሰ ከማናቸውም ነገር በማጕደል ኀጢአት ቢሠራ፣ ከመንጋው እንከን የሌለበትን አውራ በግ የበደል መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ያቅርብ። የዋጋውም ግምት በቤተ መቅደሱ ሰቅል5፥15 11.5 ግራም ይሆናል። መሠረት ተመዝኖ በጥሬ ብር ይሁን፤ ይህም የበደል መሥዋዕት ነው። 16ከተቀደሱ ነገሮች ያጐደለውንም ይተካ፤ የዚህንም ተመን አንድ አምስተኛ በላዩ ጨምሮ ለካህኑ ይስጥ፤ ካህኑም ከበጉ ጋር የበደል መሥዋዕት አድርጎ በማቅረብ ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል።
17“ ማንኛውም ሰው ኀጢአት ቢሠራ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) አታድርጉ ብሎ ከከለከላቸው ትእዛዞች ሳያውቅ አንዱን ተላልፎ ቢገኝ በደለኛ ነው፤ በኀጢአቱም ይጠየቅበታል። 18እርሱም ከመንጋው ለበደል መሥዋዕት የሚሆን እንከን የሌለበት አውራ በግ ወደ ካህኑ ያምጣ፤ ዋጋውም ተመጣጣኝ ይሁን። ካህኑም በዚህ ሁኔታ ሰውየው ሳያውቅ ስለ ፈጸመው ስሕተት ያስተሰርይለታል፤ ሰውየውም ይቅር ይባላል። 19ይህ የበደል መሥዋዕት ነው። ሰውየውም በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ጥፋት በመፈጸሙ በደለኛ5፥19 ወይም ለፈጸመው በደል ሙሉ የኀጢአቱ ማስተስረያ ነው። ነው።”
موارد قربانی گناه
1هرگاه كسی از وقوع جرمی اطلاع داشته باشد ولی در مورد آنچه كه ديده يا شنيده در دادگاه شهادت ندهد، مجرم است.
2هرگاه كسی لاشهٔ حيوان حرام گوشتی را لمس كند، حتی اگر ندانسته اين كار را كرده باشد، نجس و مجرم است.
3هرگاه كسی نجاست انسان را لمس كند، حتی اگر ندانسته اين كار را كرده باشد، وقتی متوجه شد چه كرده است، مجرم میباشد.
4اگر كسی نسنجيده قولی دهد و قسم بخورد كه آن را بجا آورد ولی بعد پی ببرد كه قول بیجايی داده است، مجرم میباشد.
5در هر يک از اين موارد، شخص بايد به گناهش اعتراف كند 6و برای قربانی گناه خود يک بره يا بز ماده نزد خداوند بياورد تا كاهن برايش كفاره كند.
7اگر شخص مجرم تنگدست باشد و نتواند برهای بياورد، میتواند دو قمری يا دو جوجه كبوتر برای كفارهٔ گناه خود به خداوند تقديم كند، يكی برای قربانی گناه و ديگری برای قربانی سوختنی. 8كاهن پرندهای را كه برای قربانی گناه آورده شده، بگيرد و سرش را ببرد، ولی طوری كه از تنش جدا نشود. 9سپس قدری از خون آن را بر پهلوی قربانگاه بپاشد و بقيه را به پای قربانگاه بريزد. اين، قربانی گناه است. 10پرندهٔ دوم را به عنوان قربانی سوختنی طبق دستورالعملی كه قبلا داده شده است قربانی كند. به اين ترتيب كاهن برای گناه او كفاره خواهد كرد و گناه او بخشيده خواهد شد.
11اگر او فقيرتر از آنست كه بتواند دو قمری يا دو جوجه كبوتر برای كفارهٔ گناه خود قربانی كند، میتواند يک كيلو آرد مرغوب بياورد. ولی نبايد آن را با روغن زيتون مخلوط كند يا كندر بر آن بگذارد، زيرا اين، قربانی گناه است. 12آرد را پيش كاهن بياورد تا كاهن مشتی از آن را به عنوان نمونه بردارد و روی قربانگاه بسوزاند، درست مثل قربانیهایی كه بر آتش به خداوند تقديم میشود. اين، قربانی گناه اوست. 13به اين ترتيب كاهن برای گناه او در هر يک از اين موارد، كفاره خواهد كرد و او بخشيده خواهد شد. در اين قربانی نيز مثل هديهٔ آردی، بقيهٔ آرد به كاهن تعلق میگيرد.
قربانی جبران
14خداوند اين دستورات را به موسی داد: 15هرگاه كسی در دادن هديهای كه در نظر خداوند مقدس است سهواً قصور ورزد، بايد يک قوچ سالم و بیعيب برای قربانی جبران به خداوند تقديم نمايد. قوچی كه برای قربانی جبران اهدا میشود بايد مطابق معيار رسمی، ارزيابی شود. 16او بايد علاوه بر باز پرداخت هديه، يک پنجم ارزش آن را نيز به آن افزوده، همه را به كاهن بدهد. كاهن با آن قوچ قربانی جبران، برايش كفاره خواهد كرد و او بخشيده خواهد شد.
17-18اگر كسی مرتكب گناهی شده، يكی از قوانين خداوند را زير پا بگذارد، ولی نداند كه چنين كاری از او سر زده است، باز مجرم است و برای قربانی جبران بايد يک قوچ سالم و بیعيب نزد كاهن بياورد. قيمت قوچ بايد مطابق قيمت تعيين شده باشد. كاهن با اين قربانی برای او كفاره كند تا گناهش بخشيده شود. 19اين قربانی جبران است برای جرمی كه او نسبت به خداوند مرتكب شده است.