ዘሌዋውያን 3 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 3:1-17

የኅብረት መሥዋዕት

1“ ‘ማንኛውም ሰው የሚያቀርበው ቍርባን ከላሞች መንጋ የሚቀርብ የኅብረት መሥዋዕት3፥1 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል፤ እንዲሁም 3፡6፡9 ይመ። ከሆነ፣ እንከን የሌለበትን ተባዕት ወይም እንስት በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርብ። 2በሚያቀርበው እንስሳ ራስ ላይ እጁን ይጫን፤ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ላይ ይረደው፤ ካህናቱም የአሮን ልጆች ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ይርጩት። 3ከኅብረት መሥዋዕቱ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ ቍርባን አድርጎ ያምጣ፤ የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ፣ በሆድ ዕቃው ላይ ያለውን ሥብ ሁሉ፣ 4ሁለቱን ኵላሊቶች፣ በኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ፣ ከኵላሊቶቹ ጋር አንድ ላይ አውጥቶ ያቅርብ። 5የአሮንም ልጆች በመሠዊያው በሚነድደው ዕንጨት ላይ ባለው በሚቃጠለው መሥዋዕት ላይ አድርገው ያቃጥሉት፤ ይህም በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ይሆናል።

6“ ‘ከበግ ወይም ከፍየሉ መንጋ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የኅብረት መሥዋዕት የሚያቀርብ ከሆነ፣ እንከን የሌለበትን ተባዕት ወይም እንስት ያቅርብ። 7መሥዋዕቱ የበግ ጠቦት ከሆነም፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያምጣው፤ 8በጠቦቱ ራስ ላይ እጁን ይጫን፤ በመገናኛው ድንኳን ፊት ለፊት ይረደው፤ የአሮንም ልጆች ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ይርጩት። 9ከኅብረት መሥዋዕቱ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ ቍርባን አድርጎ ያምጣ፤ ሥቡን፣ እስከ ጀርባ ዐጥንቱ ድረስ የተቈረጠ ላቱን በሙሉ፣ የሆድ ዕቃውን የሸፈነውን ሥብ፣ ከሆድ ዕቃው ጋር የተያያዘውን ሥብ ሁሉ፣ 10ሁለቱን ኵላሊቶች፣ ኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ ከኵላሊቶቹ ጋር አብሮ አውጥቶ ያቅርብ። 11ካህኑም ይህን ሁሉ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ የመብል ቍርባን አድርጎ በመሠዊያው ላይ ያቃጥል።

12“ ‘መሥዋዕቱ ፍየል ከሆነ፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርብ፤ 13በራሱም ላይ እጁን ይጫንበት፤ በመገናኛው ድንኳን ፊት ለፊት ይረደው፤ የአሮንም ልጆች ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ይርጩት። 14ከሚያቀርበውም መሥዋዕት ላይ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ ቍርባን አድርጎ ያቅርብ፤ የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ፣ ከሆድ ዕቃው ጋር የተያያዘውን ሥብ ሁሉ፣ 15ሁለቱን ኵላሊቶች፣ በኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ፣ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ ከኵላሊቶቹ ጋር አብሮ አውጥቶ ያቅርብ። 16ካህኑም ይህን ሁሉ በእሳት የሚቀርብና ሽታውም ደስ የሚያሰኝ የመብል ቍርባን አድርጎ በመሠዊያው ላይ ያቃጥል፤ ሥብ ሁሉ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።

17“ ‘በምትኖሩበት ስፍራ ሁሉ፣ ሥብ ወይም ደም ከቶ አትብሉ፤ ይህ ለመጪው ትውልድ ሁሉ የተሰጠ የዘላለም ሥርዐት ነው።’ ”

Persian Contemporary Bible

لاويان 3:1-17

قربانی سلامتی

1هرگاه كسی بخواهد قربانی سلامتی به خداوند تقديم كند، می‌تواند برای اين كار از گاو نر يا ماده استفاده نمايد. حيوانی كه به خداوند تقديم می‌شود بايد سالم و بی‌عيب باشد. 2شخصی كه حيوان را تقديم می‌كند، بايد دست خود را روی سر آن بگذارد و دم در خيمهٔ عبادت سرش را ببرد. پسران هارون خون آن را بر چهار طرف قربانگاه بپاشند، 3‏-5و پيه داخل شكم، قلوه‌ها و چربی روی آنها، و سفيدی روی جگر را همراه قربانی سوختنی بر آتش قربانگاه برای خداوند بسوزانند. اين هديه كه بر آتش تقديم می‌شود، مورد پسند خداوند خواهد بود.

6برای قربانی سلامتی می‌توان از گوسفند و بز (نر يا ماده) كه سالم و بی‌عيب باشد نيز استفاده كرد. 7‏-8اگر قربانی، گوسفند باشد، شخصی كه آن را به خداوند تقديم می‌كند بايد دستش را روی سر حيوان بگذارد و دم در خيمهٔ عبادت سرش را ببرد. كاهنان خون آن را بر چهار طرف قربانگاه بپاشند 9‏-11و پيه، دنبه، پيه داخل شكم، قلوه‌ها و چربی روی آنها، و سفيدی روی جگر را همچون خوراک به خداوند تقديم كرده، بر آتش قربانگاه بسوزانند.

12‏-13اگر قربانی، بز باشد، شخصی كه آن را به خداوند تقديم می‌كند بايد دستش را روی سر حيوان بگذارد و دم در خيمهٔ عبادت سرش را ببرد. كاهنان خون آن را بر چهار طرف قربانگاه بپاشند 14‏-16و پيه داخل شكم، قلوه‌ها و چربی روی آنها، و سفيدی روی جگر را همچون خوراک به خداوند تقديم كرده، بر آتش قربانگاه بسوزانند. اين هديه كه بر آتش تقديم می‌شود، مورد پسند خداوند خواهد بود. تمام پيه آن حيوان به خداوند تعلق دارد. 17هيچيک از شما نبايد خون يا پيه بخوريد. اين قانونی است ابدی برای شما و نسلهايتان، در هر جا كه باشيد.