የናዳብና የአብዩድ መሞት
1የአሮን ልጆች ናዳብና አብዩድ እያንዳንዳቸው ጥናዎቻቸውን ወስደው ፍም አደረጉባቸው፤ ዕጣንም ጨመሩባቸው፤ እርሱ ያላዘዛቸውን፣ ያልተፈቀደውን እሳት በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አቀረቡ። 2ከዚህም የተነሣ እሳት ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ዘንድ ወጥቶ በላቸው፤ በእግዚአብሔርም (ያህዌ) ፊት ሞቱ። 3ሙሴም አሮንን እንዲህ አለው፤ “እግዚአብሔር (ያህዌ)፦
“ ‘ወደ እኔ በሚቀርቡት መካከል፣
ቅድስናዬን እገልጣለሁ፤
በሕዝቡም ሁሉ ፊት፣
እከበራለሁ’
ብሎ የተናገረው ይህን ነው።” አሮንም ዝም አለ።
4ሙሴ የአሮንን አጎት የዑዝኤልን ልጆች ሚሳኤልንና ኤልጻፋንን ጠርቶ፣ “ወደዚህ ኑና ወንድሞቻችሁን አንሡ፤ ከመቅደሱም ደጃፍ አርቃችሁ፣ ከሰፈር ወደ ውጭ ውሰዷቸው” አላቸው። 5እነርሱም መጥተው ሙሴ ባዘዛቸው መሠረት፣ ሟቾቹ የክህነት ቀሚሳቸውን እንደ ለበሱ ተሸክመው ከሰፈር ወደ ውጭ አወጧቸው።
6ሙሴም አሮንንና የአሮንን ልጆች፣ አልዓዛርንና ኢታምርን እንዲህ አላቸው፤ “እንዳትሞቱ፣ በሕዝቡም ላይ ቍጣ እንዳይመጣ ጠጕራችሁን አትንጩ፤10፥6 ወይም አትላጩ ልብሳችሁንም አትቅደዱ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት ስላጠፋቸው ሰዎች ወንድሞቻችሁ እስራኤላውያን ሊያለቅሱላቸው ይችላሉ። 7የእግዚአብሔር (ያህዌ) የመቅቢያ ዘይት በላያችሁ ነውና እንዳትሞቱ ከመገናኛው ድንኳን አትውጡ።” እነርሱም ሙሴ እንዳላቸው አደረጉ።
8እግዚአብሔርም (ያህዌ) አሮንን እንዲህ አለው፤ 9“እንዳትሞቱ አንተና ልጆችህ ወደ መገናኛው ድንኳን በምትገቡበት ጊዜ የወይን ጠጅ ወይም ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጡ፤ ይህም በልጅ ልጃችሁ ዘንድ የሚጠበቅ ዘላለማዊ ሥርዐት ነው። 10የተቀደሰውንና ያልተቀደሰውን፣ ርኩሱንና ንጹሑን ለዩ፤ 11እግዚአብሔርም (ያህዌ) በሙሴ አማካይነት የሰጣቸውን ሥርዐት ሁሉ ለእስራኤላውያን አስተምሩ።”
12ሙሴም አሮንንና የተረፉትን ልጆቹን አልዓዛርንና ኢታምርን እንዲህ አላቸው፤ “በእሳት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ከቀረበው የእህል ቍርባን የቀረውን ወስዳችሁ ያለ እርሾ ጋግሩት፤ እጅግ ቅዱስ ስለሆነ በመሠዊያው አጠገብ ብሉት። 13ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት ከሚቀርበው መሥዋዕት ያንተና የልጆችህ ድርሻ ይህ ስለሆነ፣ በተቀደሰ ስፍራ ብሉት፤ እንዲህ ታዝዣለሁና። 14ከእስራኤላውያን የኅብረት መሥዋዕት10፥14 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል ላይ የእናንተ ድርሻ ሆኖ ስለ ተሰጠ፣ የተወዘወዘውን ፍርምባና የቀረበውን ወርች አንተ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆችህ በአምልኮው ሥርዐት መሠረት ንጹሕ በሆነ ስፍራ ብሉት። 15የቀረበውን ወርችና የተወዘወዘውን ፍርምባ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት የመወዝወዝ መሥዋዕት ሆኖ በእሳት ከቀረበው ሥብ ጋር ይምጣ። ይህም እግዚአብሔር (ያህዌ) ባዘዘው መሠረት ለአንተና ለልጆችህ ለዘላለም የተመደበ ድርሻ ይሆናል።”
16ሙሴ ለኀጢአት መሥዋዕት የሚቀርበውን ፍየል አጥብቆ ፈለገ፤ መቃጠሉንም በተረዳ ጊዜ የተረፉትን የአሮንን ልጆች አልዓዛርንና ኢታምርን ተቈጣቸው፤ እንዲህም አላቸው፤ 17“የኀጢአት መሥዋዕቱን ለምን በተቀደሰው ስፍራ አልበላችሁትም? እጅግ የተቀደሰ ነው፤ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ስርየት በማስገኘት የሕዝቡን ኀጢአት እንድታስወግዱበት የተሰጣችሁ ነበር፤ 18ደሙ ወደ ተቀደሰው ስፍራ ስላልገባ፣ በሰጠሁት ትእዛዝ መሠረት ፍየሉን በተቀደሰው ስፍራ መብላት ይገባችሁ ነበር።”
19አሮንም ሙሴን፣ “እነሆ፤ በዛሬው ቀን የኀጢአት መሥዋዕታቸውንና የሚቃጠል መሥዋዕታቸውን በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አቀረቡ፤ እኔም እንዲህ ያለ ነገር የደረሰብኝ ሰው ነኝ፤ ታዲያ፣ ዛሬ የኀጢአት መሥዋዕቱን ብበላ ኖሮ እግዚአብሔርስ (ያህዌ) ደስ ይለው ኖሯልን?” አለው። 20ሙሴም ይህን በሰማ ጊዜ መልሱ አረካው።
拿答和亚比户之死
1亚伦的儿子拿答和亚比户各拿自己的香炉,点火加香,在耶和华面前献上凡火。他们这样做不合耶和华的吩咐。 2于是,有火从耶和华面前出来吞噬了他们,他们就死在耶和华面前。 3摩西告诉亚伦:“耶和华曾说过,‘我要在事奉我的人10:3 “事奉我的人”希伯来文是“靠近我的人”。中显明我的圣洁,在所有子民面前彰显我的荣耀。’”亚伦默默无言。 4摩西叫来亚伦的叔父乌薛的儿子米沙利和以利撒反,对他们说:“过来,把你们弟兄的尸体从圣所前抬到营外去。” 5他们就遵照摩西的吩咐,把仍穿着内袍的尸体抬到营外。 6摩西对亚伦和他剩下的两个儿子以利亚撒和以他玛说:“你们不要蓬头散发,也不要撕裂衣服,免得你们死亡,也免得耶和华向全体会众发怒。不过,你们的所有以色列同胞都可以为耶和华用火烧死的人哀伤。 7你们不可走出会幕门口,否则你们都会死,因为耶和华的膏油在你们身上。”他们就遵照摩西的话去做。
有关祭司的条例
8耶和华对亚伦说: 9“你和你儿子们进会幕前,淡酒烈酒都不可喝,否则你们都会死。你们世世代代都要遵守这永远的条例。 10你们必须明辨什么是圣洁的、什么是世俗的,什么是洁净的、什么是不洁净的。 11你们必须将我借摩西赐给以色列人的一切律例教导他们。”
12摩西对亚伦及其两个儿子以利亚撒和以他玛说:“你们要把献给耶和华的火祭中剩下的素祭做成无酵饼,在坛边吃,因为这是至圣之物。 13你们要在圣洁之处吃,因为在献给耶和华的火祭中,这是你们和你们的子孙应得之份。这是耶和华对我的吩咐。 14至于作摇祭的胸肉和作举祭的腿肉,你们和你们的子孙可以在洁净的地方吃。因为在以色列人所献的平安祭中,这是你们应得之份。 15在献火祭的脂肪时,要把作举祭的腿肉和作摇祭的胸肉一起带到耶和华面前,这些永远是你们和你们的子孙应得之份,正如耶和华的吩咐。”
16摩西到处寻找那只作赎罪祭的公山羊,却发现那只羊已经被焚烧了。他愤怒地对亚伦剩下的两个儿子以利亚撒和以他玛说: 17“你们为什么不在圣洁之处吃这赎罪祭?这是至圣之物,耶和华赐给你们是要叫你们为会众担罪,在耶和华面前为他们赎罪。 18既然这祭牲的血没有被带进圣所,你们本应按照我的吩咐在圣洁之处吃这祭肉。” 19亚伦对摩西说:“看啊,他们今天向耶和华献赎罪祭和燔祭,却有这样的灾祸发生在我身上。今天我如果吃了这赎罪祭的祭肉,耶和华会悦纳吗?” 20摩西对亚伦的回答感到满意。