1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤
2እርሱም እንዲህ አለ፤
“እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤
ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤
የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን፤
የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”
በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ
3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣
ገለዓድን አሂዳለችና፤
4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣
በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።
5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤
በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣
በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤
የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”
ይላል እግዚአብሔር።
6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣
ለኤዶም ሸጣለችና።
7ምሽጎቿን እንዲበላ፣
በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።
8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣
የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው
እስኪሞት ድረስ፣
እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”
ይላል ጌታ እግዚአብሔር።
9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።
የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣
ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።
10ምሽጎቿን እንዲበላ፣
በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”
11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣
ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤
የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣
መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤
12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣
በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”
13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
ድንበሩን ለማስፋት፣
የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።
14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣
በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣
ምሽጎቿን እንዲበላ፣
በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።
15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣
በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”
ይላል እግዚአብሔር።
1Slova Amosova, (kterýž byl mezi pastýři) z Tekoa, kteráž viděl o Izraelovi za dnů Uziáše krále Judského, a za dnů Jeroboáma syna Joasova, krále Izraelského, dvě létě před země třesením. 2I řekl: Hospodin řváti bude z Siona, a z Jeruzaléma vydá hlas svůj, i budou kvíliti salášové pastýřů, a vyschnou pole nejvýbornější. 3Takto praví Hospodin: Pro troji nešlechetnost Damašku, ovšem pro čtveru neodpustím jemu, proto že mlátili Galáda cepami okovanými. 4Ale pošli oheň na dům Hazaelův, kterýžto zžíře paláce Benadadovy. 5I polámi závoru Damašku, a vypléním obyvatele z údolí Aven, a toho, kterýž drží berlu, z domu Eden, i půjde v zajetí lid Syrský do Kir, dí Hospodin. 6Takto praví Hospodin: Pro troji nešlechetnost Gázy, ovšem pro čtveru neslituji se nad ním, proto že je zajímajíce, v zajetí věčné podrobovali Idumejským. 7Ale pošli oheň na zed Gázy, kterýžto zžíře paláce její, 8A vypléním obyvatele z Azotu, i toho, kterýž drží berlu, z Aškalon, a obrátím ruku svou proti Akaron, i zahyne ostatek Filistinských, praví Panovník Hospodin. 9Takto praví Hospodin: Pro troji nešlechetnost Týru, ovšem pro čtveru neodpustím jemu, proto že je v zajetí věčné podrobili Idumejským, a nepamatovali na smlouvu bratrskou. 10Ale pošli oheň na zed Tyrskou, kterýžto zžíře paláce jeho. 11Takto praví Hospodin: Pro troji nešlechetnost Edoma, ovšem pro čtveru neslituji se nad ním, proto že udusiv v sobě všecku lítostivost, stihá mečem bratra svého, a hněv jeho ustavičně rozsapává, anobrž vzteklost jeho špehuje bez přestání. 12Ale pošli oheň na Teman, kterýžto zžíře paláce v Bozra. 13Toto praví Hospodin: Pro troji nešlechetnost synů Ammon, ovšem pro čtveru neodpustím jemu, proto že roztínali těhotné Galádské, jen aby rozšiřovali pomezí své. 14Ale zanítím oheň na zdi Rabba, kterýžto zžíře paláce její, s troubením v den boje a s bouří v den vichřice. 15I půjde král jejich v zajetí, on i knížata jeho s ním, praví Hospodin.