አሞጽ 1 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 1:1-15

1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2እርሱም እንዲህ አለ፤

እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤

ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤

የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን

የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”

በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣

ገለዓድን አሂዳለችና፤

4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣

በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤

በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣

በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤

የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”

ይላል እግዚአብሔር

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣

ለኤዶም ሸጣለችና።

7ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣

የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው

እስኪሞት ድረስ፣

እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።

የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣

ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤

የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣

መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣

በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ድንበሩን ለማስፋት፣

የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።

14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣

በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣

ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣

በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”

ይላል እግዚአብሔር

Swedish Contemporary Bible

Amos 1:1-15

Guds dom över Israels grannfolk

1Detta är Amos ord, som var en av herdarna från Tekoa, vad han såg angående Israel, när Ussia var kung i Juda och Jerobeam, Joashs son, var kung i Israel, två år före jordbävningen1:1 Se Sak 14:5..

2Amos sa:

Herren ryter från Sion,

från Jerusalem dånar hans röst.

Herdarnas betesmarker vissnar

och Karmels topp torkar bort.”

3Så säger Herren:

”För Damaskus tre, ja, fyra överträdelsers skull

kan jag inte låta bli att agera,

eftersom de med trösksläden av järn

har krossat Gilead.

4Jag ska sända eld mot Hasaels slott,

och den ska förtära Ben-Hadads fästningar.

5Jag ska bryta sönder bommen i Damaskus

och utplåna den som bor i Bikat-Aven

och den som bär spiran i Bet Eden.

Arams folk ska föras bort till Kir, säger Herren.”

6Så säger Herren:

”För Gazas tre, ja, fyra överträdelsers skull

kan jag inte låta bli att agera,

eftersom de fört bort hela samhällen till exil

och sålt dem till Edom.

7Jag ska sända eld mot Gazas mur,

och den ska förtära dess fästningar.

8Jag ska utplåna den som bor i Ashdod

och den som bär spiran i Ashkelon.

Jag ska vända mig mot Ekron,

tills filistéerna är döda till sista man, säger Herren, Herren.”

9Så säger Herren:

”För Tyros tre, ja, fyra överträdelsers skull

kan jag inte låta bli att agera,

eftersom de har sålt hela samhällen åt Edom

och inte tänkt på sitt broderskapsförbund.

10Jag ska sända eld mot Tyros mur,

och den ska förtära dess fästningar.”

11Så säger Herren:

”För Edoms tre, ja, fyra överträdelsers skull

kan jag inte låta bli att agera,

eftersom han har förföljt sin bror med svärd

och förkvävt sin barmhärtighet,

låtit sin vrede ständigt brinna

och sitt raseri fortsätta okontrollerat.

12Jag ska sända eld mot Teman,

och den ska förtära Bosras fästningar.”

13Så säger Herren:

”För Ammons tre, ja, fyra överträdelsers skull

kan jag inte låta bli att agera,

eftersom de skurit upp gravida kvinnor i Gilead,

då de ville utvidga sina gränser.

14Därför ska jag sätta eld på Rabbas mur,

och den ska förtära dess fästningar

under krigsrop på stridens dag,

under en våldsam vind på stormens dag.

15Deras kung måste gå till exil,

han och hans furstar tillsammans, säger Herren.”