1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤
2እርሱም እንዲህ አለ፤
“እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤
ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤
የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን፤
የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”
በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ
3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣
ገለዓድን አሂዳለችና፤
4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣
በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።
5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤
በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣
በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤
የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”
ይላል እግዚአብሔር።
6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣
ለኤዶም ሸጣለችና።
7ምሽጎቿን እንዲበላ፣
በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።
8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣
የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው
እስኪሞት ድረስ፣
እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”
ይላል ጌታ እግዚአብሔር።
9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።
የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣
ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።
10ምሽጎቿን እንዲበላ፣
በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”
11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣
ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤
የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣
መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤
12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣
በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”
13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣
ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤
ድንበሩን ለማስፋት፣
የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።
14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣
በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣
ምሽጎቿን እንዲበላ፣
በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።
15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣
በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”
ይላል እግዚአብሔር።
1De godsspraken van Amos, die tot de schaapherders van Tekóa behoorde, en zijn visioenen over Israël schouwde ten tijde van Ozias, den koning van Juda, en van Jeroboam, den zoon van Joas en koning van Israël, twee jaar voor de aardbeving. 2Hij sprak: Jahweh buldert uit Sion, Laat uit Jerusalem zijn donder rollen: De weiden der herders treuren ervan, De top van de Karmel verdort! 3Zo spreekt Jahweh! Om drie schanddaden van Damascus, Of om vier herroep Ik het niet: Omdat zij met ijzeren sleden Gilad hebben gedorst! 4Ik slinger een vuur in Chazaëls huis, Dat de burchten van Ben-Hadad verteert; 5Ik sla de grendel van Damascus aan stukken, Roei de bewoners van het “Dal der Ongerechtigheid”, uit, Den scheptervoerder van het “Huis van Geneugte”, Arams bevolking zal naar Kir in ballingschap gaan: Spreekt Jahweh! 6Zo spreekt Jahweh! Om drie schanddaden van Gaza, Of om vier herroep Ik het niet: Omdat zij heel een bevolking hebben weggevoerd, Om ze aan Edom te verkopen! 7Ik slinger een vuur binnen de muren van Gaza, Dat zijn burchten verteert; 8Ik roei de bewoners van Asjdod uit, Den scheptervoerder van Asjkelon; Ik strek mijn hand tegen Ekron uit, Wat van de Filistijnen nog rest, gaat te gronde: Spreekt Jahweh, de Heer! 9Zo spreekt Jahweh! Om drie schanddaden van Tyrus, Of om vier herroep Ik het niet: Omdat zij heel een bevolking aan Edom hebben verkocht, Zich aan het broeder-verbond niet hebben gestoord! 10Ik slinger een vuur binnen de muren van Tyrus, Dat zijn burchten verteert! 11Zo spreekt Jahweh! Om drie schanddaden van Edom, Of om vier herroep Ik het niet: Omdat hij zijn broeder met het zwaard heeft vervolgd, En zijn medelijden verstikt, Altijd maar wraak heeft gekoesterd, Zijn gramschap eeuwig liet duren! 12Ik slinger een vuur in Teman, Dat de burchten van Bosra verteert! 13Zo spreekt Jahweh! Om drie schanddaden van de zonen van Ammon, Of om vier herroep Ik het niet: Omdat zij Gilads zwangere vrouwen hebben opengereten, Om hun eigen gebied te vergroten! 14Ik ontsteek een vuur binnen de muren van Rabba, Dat zijn burchten verteert: Onder gehuil op de dag van de strijd, Onder geloei op de dag van de storm; 15Ook hun koning zal in ballingschap gaan, Tegelijk met zijn vorsten: Spreekt Jahweh!