ናሆም 3 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ናሆም 3:1-19

ለነነዌ

1ለደም ከተማ ወዮላት!

ሐሰት፣ ዘረፋም ሞልቶባታል፤

ብዝበዛዋ ተግዞ አያልቅም።

2የጅራፍ ድምፅ፣

የመንኰራኵር ኳኳቴ፣

የፈጣን ፈረስ ኰቴ፣

የሠረገሎች ድምፅ ተሰምቷል።

3ፈረሰኛው ይጋልባል፤

ሰይፍ ይንቦገቦጋል፤

ጦር ያብረቀርቃል።

የሞተው ብዙ ነው፤

ሬሳ በሬሳ ሆኗል፤

ስፍር ቍጥር የለውም፤

መተላለፊያ አልተገኘም።

4ይህ ሁሉ የሆነው ቅጥ ባጣች፣

አሳሳችና መተተኛ በሆነች ዘማዊት ምክንያት ነው፤

እርሷም በዝሙቷ አሕዛብን፣

በጥንቈላዋም ሕዝቦችን ባሪያ ያደረገች ናት።

5የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እኔ በጠላትነት ተነሥቼብሻለሁ፤

ቀሚስሽን እስከ ፊትሽ እገልበዋለሁ፤

ዕርቃንሽን ለአሕዛብ፣

ኀፍረትሽንም ለነገሥታት አሳያለሁ።

6ቈሻሻ እደፋብሻለሁ፤

እንቅሻለሁ፤

ማላገጫም አደርግሻለሁ።

7የሚያዩሽ ሁሉ ከአንቺ እየሸሹ፣

‘ነነዌ ፈራርሳለች፤ ማን ያለቅስላታል?’ ይላሉ፤

የሚያጽናናሽንስ ከወዴት አገኛለሁ?”

8አንቺ በአባይ ወንዝ አጠገብ ካለችው፣

በውሃ ከተከበበችው፣

ከኖእ አሞን3፥8 አንዳንዶች ቴብስ ይላሉ። ትበልጫለሽን?

ወንዙ መከላከያዋ፣

ውሃውም ቅጥሯ ነው።

9ኢትዮጵያና ግብፅ ወሰን የለሽ ኀይሏ ናቸው፤

ፉጥና ሊቢያም ረዳቶቿ ነበሩ።

10ይሁን እንጂ በምርኮ ተወሰደች፤

ተሰድዳም ሄደች።

በየመንገዱ ማእዘን ላይ፣

ሕፃናቷ ተፈጠፈጡ፤

በመሳፍንቷ ላይ ዕጣ ተጣለ፤

ታላላቅ ሰዎቿ ሁሉ በሰንሰለት ታሰሩ።

11አንቺ ደግሞ ትሰክሪአለሽ፤

ትደበቂአለሽ፣

ከጠላትም መሸሸጊያ ትፈልጊአለሽ።

12ምሽጎችሽ ሁሉ ሊበሉ እንደ ደረሱ

የመጀመሪያ በለስ ፍሬ ናቸው፤

በሚወዛወዙበት ጊዜ፣

ፍሬዎቹ በበላተኛው አፍ ውስጥ ይወድቃሉ።

13እነሆ፤ ጭፍሮችሽ፣

ሁሉም ሴቶች ናቸው!

የምድርሽ በሮች፣

ለጠላቶችሽ ወለል ብለው ተከፍተዋል፤

መዝጊያዎቻቸውንም እሳት በልቷቸዋል።

14ለከበባው ውሃ ቅጅ፤

መከላከያሽን አጠናክሪ፤

የሸክላውን ዐፈር ፈልጊ፤

ጭቃውን ርገጪ፤

ጡቡንም ሥሪ።

15በዚያ እሳት ይበላሻል፤

ሰይፍ ይቈርጥሻል፤

እንደ ኵብኵባም ይግጥሻል።

እንደ ኵብኵባ እርቢ፤

እንደ አንበጣም ተባዢ።

16ከሰማይ ከዋክብት እስኪበልጡ ድረስ፣

የነጋዴዎችሽን ቍጥር አበዛሽ፤

ምድሪቱን ግን እንደ አንበጣ ግጠው አሟጠጡ፤

ከዚያም በርረው ሄዱ።

17ጠባቂዎችሽ እንደ አንበጣ፣

መኳንንትሽም በብርድ ቀን

በቅጥር ሥር እንደሚቀመጥ ኵብኵባ ናቸው፤

ፀሓይ ሲወጣ ግን ይበርራሉ፤

የት እንደሚበርሩም አይታወቅም።

18የአሦር ንጉሥ ሆይ፤ እረኞችህ3፥18 ገዦች ማለት ነው። አንቀላፉ፤

መኳንንትህ ዐርፈው ተኙ፤

ሕዝብህ ሰብሳቢ ዐጥተው፣

በተራራ ላይ ተበትነዋል።

19ቍስልህን ሊፈውስ የሚችል የለም፤

ስብራትህም ለሞት የሚያደርስ ነው።

ስለ አንተ የሰማ ሁሉ፣

በውድቀትህ ደስ ብሎት ያጨበጭባል፤

ወሰን የሌለው ጭካኔህ

ያልነካው ማን አለና?

Korean Living Bible

나훔 3:1-19

니느웨에 미칠 화

1피의 성에 화가 있을 것이다. 사기와 약탈이 판을 치고 있으므로 희생자가 떠 날 날이 없다.

2휙휙하는 채찍 소리, 덜거덩거리는 전차 바퀴 소리, 뛰는 말과 달리는 전차,

3격돌하는 기병, 번쩍이는 칼, 빛나는 창, 수많은 사상자, 시체더미, 헤아릴 수 없는 주검들, 시체에 걸려 넘어지는 사람들!

4이 모든 것은 니느웨가 요염한 창녀처럼 음행하였기 때문이다. 저가 음행으로 여러 나라를 사로잡고 마력으로 그 백성을 미혹하였다.

5전능하신 여호와께서 말씀하신다. “니느웨야, 내가 너를 대적하여 네 치마를 네 얼굴까지 걷어올려 너의 벌거벗은 수치를 온 세계에 보일 것이다.

6내가 또 더러운 것을 너에게 던져 너를 모욕하고 너를 구경거리가 되게 하겠다.

7너를 보는 자들이 다 네게서 도망하며 ‘니느웨가 황폐하였다. 누가 너를 위해 슬피 울까?’ 하고 말할 것이다. 너를 위로할 자를 내가 어디서 구할 수 있겠는가?”

8네가 3:8 원문에는 ‘노아몬’데베스보다 나은가? 그는 나일 강가에 위치하여 물로 둘러싸였으므로 강이 방어선이 되고 물이 성벽이 되었으며

93:9 원문에는 ‘구스’에티오피아와 이집트가 그에게 강력한 힘이 되었고 붓과 3:9 히 ‘루빔’리비아도 그의 동맹국이 되었다.

10그런데도 그는 포로가 되어 사로잡혀갔으며 그 어린 아이들은 길 모퉁이에 내동댕이침을 당해 박살이 났고 귀족들은 종으로 팔려가기 위해 제비 뽑혔으며 모든 지도급 인사들은 사슬에 묶였으니

11너도 취하게 될 것이며 네 대적을 피하여 숨을 곳을 찾게 될 것이다.

12무화과나무의 처음 익은 열매가 흔들기만 하면 먹는 자의 입에 떨어지듯이 너의 모든 요새들이 쉽게 무너질 것이다.

13너의 병사들을 보아라. 그들은 여자처럼 무력하다! 네 땅의 성문들이 네 대적 앞에 활짝 열려 있으니 그 빗장들이 불에 탈 것이다.

14너는 포위당할 일에 대비하여 물을 길어 두고 방어진을 튼튼하게 하며 진흙을 밟아 벽돌 가마를 수리하라.

15그러나 3:15 암시됨.네가 아무리 방비하여도 불이 너를 삼키며 칼이 너를 베고 메뚜기떼가 곡식을 먹어가듯이 네 대적이 너를 먹을 것이다. 메뚜기떼처럼 네 인구수를 많게 해 보아라.

16네가 네 상인들의 수를 하늘의 별처럼 많게 하였으나 메뚜기처럼 다 날아가 버리고 말았다.

17너의 병사들과 지휘관들은 추운 날 울타리에 깃들였다가 해가 뜨면 날아가 버리는 메뚜기떼와 같아서 아무도 그들이 간 곳을 알지 못한다.

18앗시리아 왕아, 네 목자들은 죽었고 네 귀족들도 영원히 잠들었으며 네 백성들은 산에 흩어졌는데도 그들을 모을 자가 없다.

19네가 중상을 입었으므로 아무도 네 상처를 고칠 수 없다. 네 소식을 듣는 자들이 다 기뻐서 손뼉을 치고 있으니 잔학한 너에게 피해를 입지 않은 자가 아무도 없기 때문이다.