ምሳሌ 3 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 3:1-35

ከጥበብ የሚገኝ ተጨማሪ በረከት

1ልጄ ሆይ፤ ትምህርቴን አትርሳ፤

ትእዛዞቼን በልብህ ጠብቅ፤

2ቀኖችን ይጨምሩልሃል፤ ዓመቶችንም ያረዝሙልሃል፤

ሕይወት፣ ሀብትንና ሰላምን ያበዙልሃል።

3ፍቅርና ታማኝነት ከቶ አይለዩህ፤

በዐንገትህ ዙሪያ እሰራቸው፤

በልብህም ጽላት ላይ ጻፋቸው።

4በዚያን ጊዜ ሞገስንና መልካም ስምን፣

በእግዚአብሔርና በሰው ዘንድ ታገኛለህ።

5በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፤

በራስህ ማስተዋል አትደገፍ፤

6በመንገድህ ሁሉ እርሱን ዕወቅ፤

እርሱም ጐዳናህን ቀና ያደርገዋል።3፥6 ወይም ጐዳናህን ያቀናልሃል

7በራስህ አስተያየት ጠቢብ ነኝ አትበል፤

እግዚአብሔርን ፍራ፤ ከክፉም ራቅ።

8ይህም ለሰውነትህ ጤንነትን፣

ለዐጥንትህም ልምላሜን ያመጣልሃል።

9እግዚአብሔርን በሀብትህ፣

ከምርትህ ሁሉ በኵራት አክብረው፤

10ይህን ብታደርግ፣ ጎተራህ ሞልቶ ይትረፈረፋል፤

መጥመቂያህም በአዲስ የወይን ጠጅ ቲፍ ብሎ ይሞላል።

11ልጄ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ተግሣጽ አትናቅ፤

በዘለፋውም አትመረር፤

12አባት ደስ የሚሰኝበትን ልጁን እንደሚቀጣ3፥12 ወይም እንደሚገሥጽ ሁሉ፣

እግዚአብሔርም የሚወድደውን ይገሥጻልና።

13ጥበብን የሚያገኛት፣

ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርጋት ሰው ቡሩክ ነው፤

14እርሷ ከብር ይልቅ ትርፍ የምታመጣ፣

ከወርቅም ይልቅ ጥቅም የምታስገኝ ናትና።

15ከቀይ ዕንይበልጥ ውድ ናት፤

አንተ ከምትመኘውም ሁሉ የሚስተካከላት የለም።

16በቀኝ እጇ ረዥም ዕድሜ አለ፤

በግራ እጇም ሀብትና ክብር ይዛለች።

17መንገዷ ደስ የሚያሰኝ ነው፤

ጐዳናዋም ሁሉ ሰላም ነው።

18ለሚያቅፏት የሕይወት ዛፍ ናት፤

የሚይዟትም ይባረካሉ።

19እግዚአብሔር በጥበብ ምድርን መሠረተ፤

በማስተዋል ሰማያትን በየስፍራቸው አጸና፤

20በዕውቀቱ ቀላያት ተከፈሉ፤

ደመናትም ጠልን አንጠበጠቡ።

21ልጄ ሆይ፤ ትክክለኛ ፍርድንና አስተውሎ መለየትን ጠብቅ፤

እነዚህ ከእይታህ አይራቁ፤

22ለነፍስህ ሕይወት፣

ለዐንገትህም ጌጥ ይሆናሉ።

23ከዚያም መንገድህን በሰላም ትሄዳለህ፤

እግርህም አይሰናከልም፤

24ስትተኛ አትፈራም፤

ትተኛለህ እንቅልፍህም ጣፋጭ ይሆናል።

25ድንገተኛን መከራ፣

በክፉዎች ላይ የሚደርሰውንም ጥፋት አትፍራ፤

26እግዚአብሔር መታመኛህ ይሆናልና፤

እግርህንም በወጥመድ ከመያዝ ይጠብቃል።

27ማድረግ እየቻልህ

ለሚገባቸው መልካም ነገር ከማድረግ አትቈጠብ።

28አሁን በእጅህ እያለ፣

ጎረቤትህን፣ “ቈይተህ ተመለስ፤ ነገ እሰጥሃለሁ” አትበለው።

29አንተን ተማምኖ በአጠገብህ በተቀመጠ፣

በጎረቤትህ ላይ ክፉ አትምከርበት።

30ምንም ጕዳት ሳያደርስብህ፣

ያለ ምክንያት ሰውን አትክሰስ።

31በክፉ ሰው አትቅና፤

የትኛውንም መንገዱን አትምረጥ፤

32እግዚአብሔር ጠማማን ሁሉ ይጸየፋልና፤

ለቅን ሰው ግን ምስጢሩን ይገልጥለታል።

33የእግዚአብሔር ርግማን በክፉዎች ቤት ላይ ነው፤

የጻድቃንን ቤት ግን ይባርካል።

34እርሱ በዕቡያን ፌዘኞች ላይ ያፌዛል፤

ለትሑታን ግን ሞገስን ይሰጣል።

35ጠቢባን ክብርን ይወርሳሉ፤

ሞኞችን ግን ለውርደት ያጋልጣቸዋል።

Korean Living Bible

잠언 3:1-35

젊은이들에게 주는 교훈

1내 아들아, 나의 가르침을 잊지 말고 내 명령을 정성껏 지켜라.

2그러면 네가 장수하고 평안을 누릴 것이다.

3너는 사랑과 성실이 너를 떠나지 않게 하며 그것을 네 목에 매고 네 마음에 새겨라.

4그러면 네가 하나님과 사람 앞에서 사랑과 신망을 얻을 것이다.

5너는 마음을 다하여 여호와를 신뢰하고 3:5 또는 ‘네 명철을’네 지식을 의지하지 말아라.

6너는 모든 일에 여호와를 인정하라. 그러면 그가 너에게 바른 길을 보이실 것이다.

7스스로 지혜롭다고 생각하지 말아라. 너는 여호와를 두려워하고 악을 피하라.

8이것이 너에게 좋은 약이 되어 3:8 또는 ‘네 골수로 윤택하게 하리라’너의 몸과 마음을 건강하게 할 것이다.

9네 재산과 네 모든 농산물의 첫열매로 여호와를 공경하라.

10그러면 네 창고가 가득 차고 포도주통에 새 포도주가 넘칠 것이다.

11내 아들아, 여호와의 징계를 가볍게 여기지 말며 그의 꾸지람을 언짢게 생각하지 말아라.

12아버지가 자식이 잘되라고 꾸짖고 나무라는 것처럼 여호와께서도 자기가 사랑하는 사람을 꾸짖고 나무라신다.

13지혜와 깨달음을 가진 자는 행복하다.

14그것이 은이나 금보다 더 가치 있고 유익하기 때문이다.

15지혜는 보석보다 더 귀한 것이므로 네가 갖고 싶어하는 그 어떤 것도 이것과 비교가 되지 않는다.

16그 오른손에는 장수가 있고 그 왼손에는 부귀가 있으니

17그 길은 즐거움과 평안의 길이다.

18지혜는 그것을 얻은 자에게 생명 나무와도 같은 것이다. 그래서 지혜를 가진 자가 복이 있다.

19여호와께서는 지혜로 땅의 기초를 놓으셨으며 3:19 또는 ‘명철로’예지로 우주 공간을 펼치셨고

20지식으로 깊은 물을 나누시고 공중에서 이슬이 내리게 하셨다.

21내 아들아, 건전한 지혜와 분별력을 잘 간직하고 그것이 네게서 떠나지 않게 하라.

22그러면 그것이 네 영혼의 생명이 되고 3:22 또는 ‘네 목에 장식이 되리니’네 삶을 아름답게 장식할 것이니

23네가 네 길을 안전하게 갈 수 있고 발이 걸려 넘어지는 일도 없을 것이며

24잠자리에 들 때 두려워하지 않고 단잠을 잘 수 있을 것이다.

25너는 갑자기 밀어닥친 재앙이나 악인들의 멸망이 이를 때 두려워하지 말아라.

26여호와는 네가 의지할 분이시니 너를 안전하게 지키실 것이다.

27선을 베풀 능력이 있거든 그것을 필요로 하는 자에게 베풀기를 주저하지 말며

28너에게 가진 것이 있으면 네 이웃에게 “갔다가 다시 오너라. 내일 주겠다” 라고 말하지 말아라.

29너를 믿고 사는 네 이웃을 해하려고 계획하지 말며

30남이 너를 해하지 않았거든 이유 없이 다투지 말아라.

31난폭한 자를 부러워하지 말며 그의 어떤 행동도 본받지 말아라.

32여호와께서는 악한 자를 미워하시고 정직한 자와 친근히 하신다.

33악인의 집에는 여호와의 저주가 있으나 의로운 자의 집에는 축복이 있다.

34여호와는 거만한 자를 비웃으시고 겸손한 사람에게 은혜를 베푸신다.

35지혜로운 자는 영광을 얻을 것이나 미련한 자는 수치를 당할 것이다.