ምሳሌ 21 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 21:1-31

1የንጉሥ ልብ በእግዚአብሔር እጅ ነው፤

እርሱም እንደ ቦይ ውሃ ደስ ወዳሰኘው ይመራዋል።

2ለሰው መንገዱ ሁሉ ቀና ይመስለዋል፤

እግዚአብሔር ግን ልብን ይመዝናል።

3ከመሥዋዕት ይልቅ ጽድቅንና ፍትሕን ማድረግ፣

በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አለው።

4ትዕቢተኛ ዐይን፣ እብሪተኛ ልብ፣

የክፉዎችም መብራት ኀጢአት ናቸው።

5የትጉህ ሰው ዕቅድ ወደ ትርፍ ያመራል፤

ችኰላም ወደ ድኽነት ያደርሳል።

6በሐሰተኛ አንደበት የተገኘ ሀብት፣

በንኖ የሚጠፋ ተን፣ ለሞትም የሚያበቃ ወጥመድ ነው።21፥6 አንዳንድ የዕብራይስጥ ጽሑፎች፣ የሰብዓ ሊቃናትና የቩልጌት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አያሌ የዕብራይስጥ ጽሑፎች ግን ሞትን ለሚሹ በንኖ እንደሚጠፋ ተን ነው ይላሉ።

7ክፉዎችን ዐመፃቸው ይጠራርጋቸዋል፤

ቅን ነገር ማድረግ አይወድዱምና።

8የበደለኛ መንገድ ጠማማ ነው፤

የንጹሕ ሰው ጠባይ ግን ቀና ነው።

9ከጨቅጫቃ ሚስት ጋር በአንድ ቤት ከመኖር፣

በጣራ ላይ ጥግ ይዞ መኖር ይሻላል።

10ክፉ ሰው ክፋትን አጥብቆ ይመኛል፤

ባልንጀራውም ከእርሱ ዘንድ ርኅራኄን አያገኝም።

11ፌዘኛ ሲቀጣ፣ አላዋቂ ጥበብን ያተርፋል፤

ጠቢብ ሰው ቢማር ዕውቀትን ያገኛል።

12ጻድቁ21፥12 ወይም ጻድቁ ሰው የክፉዎችን ቤት ልብ ብሎ ይመለከታል፤

ክፉዎችንም ያጠፋቸዋል።

13ሰው የድኾችን ጩኸት ላለመስማት ጆሮውን ቢዘጋ፣

እርሱም ይጮኻል፤ መልስም አያገኝም።

14በስውር የተደረገ ስጦታ ቍጣን ያበርዳል፤

በጕያ የተሸሸገ እጅ መንሻም ታላቅ ቍጣን ጸጥ ያደርጋል።

15ፍትሕ ሲሰፍን ጻድቁን ደስ ያሰኘዋል፤

ክፉ አድራጊዎችን ግን ያሸብራል።

16የማስተዋልን መንገድ የሚስት ሰው፣

በሙታን ጉባኤ ያርፋል።

17ቅንጦትን የሚወድድ ይደኸያል፤

የወይን ጠጅና ዘይት የሚወድድም ባለጠጋ አይሆንም።

18ክፉ ሰው ለጻድቅ፣

ወስላታም ለቅን ሰው ወጆ ይሆናል።

19ከጨቅጫቃና ከቍጡ ሚስት ጋር ከመኖር፣

በምድረ በዳ መኖር ይሻላል።

20በጠቢብ ቤት ምርጥ ምግብና ዘይት ተከማችቶ ይገኛል፤

ተላላ ሰው ግን ያለ የሌለውን ያሟጥጣል።

21ጽድቅንና ፍቅርን የሚከተል፤

ሕይወትን ብልጽግናንና21፥21 ወይም ጽድቅን ክብርን ያገኛል።

22ጠቢብ የኀያላንን ከተማ ቅጥር ጥሶ ይገባል፤

መታመኛ ምሽጋቸውንም ያፈርሳል።

23አንደበቱንና ምላሱን የሚቈጣጠር፣

ራሱን ከመቅሠፍት ይጠብቃል።

24ትዕቢተኛና ኵሩ ሰው “ፌዘኛ” ይባላል፤

በጠባዩም እብሪተኛ ነው።

25ታካችን የሚገድለው ምኞቱ ነው፤

እጆቹ መሥራት አይፈልጉምና።

26ክፉ ሰው ቀኑን ሙሉ ይመኛል፤

ጻድቅ ግን አንዳች ሳያስቀር ይሰጣል።

27የክፉ ሰው መሥዋዕት አስጸያፊ ነው፤

በክፉ ዐላማ ሲያቀርብማ የቱን ያህል አስከፊ ይሆን!

28ሐሰተኛ ምስክር ይጠፋል፤21፥28 ወይም የታዛዥ ሰው ቃል ግን ጸንቶ ይኖራል

እውነቱን የሚናገር ግን ጸንቶ ይኖራል።

29ክፉ ሰው በዐጕል ድፍረት ይቀርባል፤

ቅን ሰው ግን አደራረጉን ያስተውላል።

30እግዚአብሔርን ለመቋቋም የሚያስችል፣

አንዳችም ጥበብ፣ ማስተዋልና ዕቅድ የለም።

31ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤

ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

Japanese Contemporary Bible

箴言 知恵の泉 21:1-31

21

1灌漑の水が流れ込むように、

主は王の心を思いのままに動かされます。

2どんな行いでも、

もっともらしい理由をつければ正しく見えますが、

神はどんなつもりでそうしたかを見ます。

3供え物をするより、

正しい人であるほうが主に喜ばれます。

4高慢も、情欲も、

悪い行いも、みな罪です。

5地道に努力すれば利益がもたらされ、

一儲けしようと急ぐと貧困がもたらされます。

6不正で得た富はすぐなくなります。

それなのになぜ、危険を冒そうとするのでしょう。

7悪者は不正を行ってばかりいますが、

いずれその悪事が戻ってきて、

自分を滅ぼすことになります。

8行いを見ればその人がわかります。

悪人は悪いことをし、

正しい人は神の教えを守るのです。

9怒りっぽい女とりっぱな家に住むより、

屋根裏部屋の隅で暮らすほうがましです。

10悪人は人を傷つけるのが大好きで、

人に親切にしようなどとは考えもしません。

11知恵のある人は聞くだけで学ぶことができます。

愚か者は、人をばかにする者が罰を受けるのを

見るまでは、学ぶことができません。

12正しい方である神は、

悪者が家の中で何をしているのか知っていて、

その者にさばきを下します。

13貧しい人を助けない者は、

自分が困ったときにも助けてもらえません。

14贈り物をすれば、怒っている人も機嫌を直します。

15正しい人は喜んで正しいことをし、

悪人を恐れさせます。

16わきまえのない怠け者は、

のたれ死にするしかありません。

17毎日遊び暮らしていると貧しくなります。

酒やぜいたく品は富をもたらしません。

18最後に勝つのは、悪人ではなく正しい人です。

19口うるさく不平ばかりこぼす女といるより、

荒野に住むほうがましです。

20知恵のある人は将来に備えて貯金をし、

愚か者は考えもなしに金を使います。

21正しく思いやりのある者になろうとする人は、

充実した生活を送り、人からもたたえられます。

22知恵のある人は強い相手と戦っても負けません。

とりでに立てこもる敵も見事に打ち負かします。

23口を開かないでいれば、

苦難に陥ることもありません。

24人をばかにする者は傲慢で、

自分が一番だと思い上がっています。

25-26怠け者は働きもしないで、やたらに欲しがり、

人をうらやむことしか知りません。

しかし神を恐れる人は、喜んで人に与えます。

27神は悪人からの贈り物がきらいです。

何か下心があるときはなおさらです。

28偽証すれば罰せられ、正直に証言すれば安全です。

29悪人は強情ですが、

神を恐れる人は、悪いとわかれば素直に考え直します。

30どんなに賢明な人でも、

どんなに良い教育を受けた人でも、

主と対等にやり合うことなどできません。

31さあ、戦う準備をしなさい。

しかし、勝利は主によってもたらされます。