ሚልክያስ 1 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ሚልክያስ 1:1-14

1በሚልክያስ1፥1 ሚልክያስ የስሙ ትርጕም መልእክተኛዬ ማለት ነው። በኩል ወደ እስራኤል የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ንግር ይህ ነው፤

ያዕቆብ ተወደደ፤ ዔሳው ተጠላ

2“እኔ ወድጃችኋለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “እናንተ ግን፣ ‘እንዴት ወደድኸን?’ ትላላችሁ።”

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ዔሳው የያዕቆብ ወንድም አልነበረምን? ያዕቆብን ወደድሁት፤ 3ዔሳውን ግን ጠላሁት፤ ተራሮቹን ባድማ አደረግሁ፤ ርስቱንም ለምድረ በዳ ቀበሮዎች ሰጠሁበት።”

4ኤዶምያስ፣ “ብንደመሰስም እንኳ የፈረሰውን መልሰን እንሠራዋለን” ይል ይሆናል። እግዚአብሔር ጸባኦት ግን እንዲህ ይላል፤ “እነርሱ ይሠሩ ይሆናል፤ እኔ ግን አፈርስባቸዋለሁ፤ ክፉ ምድር፣ እግዚአብሔርም ለዘላለም የተቈጣው ሕዝብ ተብለው ይጠራሉ። 5ይህንም በገዛ ዐይናችሁ ታያላችሁ፤ እናንተም፣ ‘ከእስራኤል ዳርቻ ወዲያ እንኳ እግዚአብሔር ታላቅ ነው!’ ትላላችሁ።

እንከን ያለበት መሥዋዕት

6“ልጅ አባቱን፣ ባሪያም ጌታውን ያከብራል፤ እኔ አባት ከሆንሁ፣ መከበሬ የት አለ? ጌታስ ከሆንሁ መፈራቴ የት አለ?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት፤ ካህናት ሆይ፤ ስሜን የምታቃልሉት እናንተ ናችሁ።

“እናንተ ግን፣ ‘ስምህን ያቃለልነው እንዴት ነው?’ ትላላችሁ።

7“በመሠዊያዬ ላይ የረከሰ ምግብ ታስቀምጣላችሁ።

“እናንተ ግን፣ ‘ያረከስንህ እንዴት ነው?’ አላችሁ።

የእግዚአብሔር ገበታ የተናቀ ነው በማለታችሁ ነው። 8የታወረውን እንስሳ ለመሥዋዕት ስታቀርቡ፣ ያ በደል አይደለምን? ዐንካሳውን ወይም በሽተኛውን እንስሳ መሥዋዕት አድርጋችሁ ስታቀርቡ፣ ያስ በደል አይደለምን? ያንኑ ለገዣችሁ ብታቀርቡ፣ በእናንተ ደስ ይለዋልን? ወይስ ይቀበለዋልን?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

9“አሁን ግን እንዲራራልን እግዚአብሔርን ለምኑ፤ እንደዚህ ዐይነቱን መሥዋዕት ይዛችሁ ስትቀርቡ ይቀበላችኋልን?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 10“በመሠዊያዬ ላይ ከንቱ እሳት እንዳታነድዱ፣ ምነው ከእናንተ አንዱ የቤተ መቅደሱን ደጅ በዘጋ ኖሮ! እኔ በእናንተ ደስ አይለኝም፤ ከእጃችሁም ምንም ዐይነት ቍርባን አልቀበልም” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 11“ከፀሓይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ፣ ስሜ በሕዝቦች መካከል የከበረ ይሆናል፤ በየስፍራውም ሁሉ ለስሜ ዕጣንና ንጹሕ ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በሕዝቦች መካከል የከበረ ይሆናልና” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

12“እናንተ ግን የእግዚአብሔር ገበታ፣ ‘ርኩስ ነው’ ምግቡም፣ ‘የተናቀ ነው’ በማለት ታቃልላላችሁ። 13ደግሞም፣ ‘ይህ ድካም ነው’ በማለት በንቀት ጢቅ አላችሁበት” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

“በቅሚያ የመጣውን፣ ዐንካሳውንና የታመመውን እንስሳ ቍርባን አድርጋችሁ ስታቀርቡ ከእጃችሁ መቀበል ይገባኛልን?” ይላል እግዚአብሔር14“በመንጋው ውስጥ ተቀባይነት ያለው ተባዕት በግ ኖሮት ይህንኑ ሊሰጥ ተስሎ ሳለ፣ በማታለል ነውር ያለበትን እንስሳ ለጌታ የሚሠዋ ርጉም ይሁን፤ እኔ ታላቅ ንጉሥ ነኝ፤ ስሜም በሕዝቦች ዘንድ ሊፈራ የሚገባ ነውና” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

New International Reader’s Version 2014

Malachi 1:1-14

1This is a prophecy. It is the Lord’s message to Israel through Malachi.

Israel Doubts God’s Love

2“Israel, I have loved you,” says the Lord.

“But you ask, ‘How have you loved us?’

“Wasn’t Esau Jacob’s brother?” says the Lord. “But I chose Jacob 3instead of Esau. I have turned Esau’s hill country into a dry and empty land. I left that land of Edom to the wild dogs in the desert.”

4Edom might say, “We have been crushed. But we’ll rebuild our cities.”

The Lord who rules over all says, “They might rebuild their cities. But I will destroy them. They will be called the Evil Land. My anger will always remain on them. 5You will see it with your own eyes. You will say, ‘The Lord is great! He rules even beyond the borders of Israel!’

Give Your Best to the Lord

6“A son honors his father. A slave honors his master. If I am a father, where is the honor I should have? If I am a master, where is the respect you should give me?” says the Lord who rules over all.

“You priests look down on me.

“But you ask, ‘How have we looked down on you?’

7“You sacrifice ‘unclean’ food on my altar.

“But you ask, ‘How have we made you “unclean”?’

“You do it by looking down on my altar. 8You sacrifice blind animals to me. Isn’t that wrong? You sacrifice disabled or sick animals. Isn’t that wrong? Try offering them to your governor! Would he be pleased with you? Would he accept you?” says the Lord who rules over all.

9“Now plead with God to be gracious to us! But as long as you give offerings like those, how can he accept you?” says the Lord.

10“You might as well shut the temple doors! Then you would not light useless fires on my altar. I am not pleased with you,” says the Lord. “I will not accept any of the offerings you bring. 11My name will be great among the nations. They will worship me from where the sun rises in the east to where it sets in the west. In every place, incense and pure offerings will be brought to me. That’s because my name will be great among the nations,” says the Lord.

12“But you treat my name as if it were not holy. You say the Lord’s altar is ‘unclean.’ And you look down on its food. 13You say, ‘What a heavy load our work is!’ And you turn up your nose. You act as if you hate working for me,” says the Lord who rules over all.

“You bring animals that have been hurt. Or you bring disabled or sick animals. Then you dare to offer them to me as sacrifices! Should I accept them from you?” says the Lord. 14“Suppose you have a male sheep or goat that does not have any flaws. And you promise to offer it to me. But then you sacrifice an animal that has flaws. When you do that, you cheat me. And anyone who cheats me is under my curse. After all, I am a great king,” says the Lord who rules over all. “The other nations have respect for my name. So why don’t you respect it?