ሆሴዕ 12 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 12:1-14

1ኤፍሬም የነፋስ እረኛ ነው፤

ቀኑን ሙሉ የምሥራቅን ነፋስ ይከተላል፤

ሐሰትንና ዐመፅን ያበዛል።

ከአሦር ጋር ቃል ኪዳን ያደርጋል፤

የወይራ ዘይትንም ወደ ግብፅ ይልካል።

2እግዚአብሔር በይሁዳ ላይ የሚያቀርበው ክስ አለው፤

ያዕቆብን12፥2 ያዕቆብ ማለት ተረከዝ ይይዛል ማለት ሲሆን፣ ያታልላል ለማለት ዘይቤአዊ አገላለጽ ነው። እንደ መንገዱ ይቀጣዋል፤

እንደ ሥራውም ይከፍለዋል።

3በማሕፀን ሳለ የወንድሙን ተረከዝ ያዘ፤

ሙሉ ሰውም ሲሆን ከአምላክ ጋር ታገለ።

4ከመልአኩም ጋር ታገለ፤ አሸነፈውም፤

በፊቱ ሞገስን ለማግኘት አልቅሶ ለመነው፣

እርሱንም በቤቴል አገኘው፤

በዚያም ከእርሱ ጋር ተነጋገረ፤

5እርሱም ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር

የሚታወቅበት ስሙም እግዚአብሔር ነው።

6ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤

ፍቅርንና ፍትሕን ጠብቅ፤

ዘወትርም በአምላክህ ታመን።

7ነጋዴው በሐሰተኛ ሚዛን ይሸጣል፤

ማጭበርበርንም ይወድዳል።

8ኤፍሬም እንዲህ እያለ ይታበያል፤

“እኔ ባለጠጋ ነኝ፤ ሀብታምም ሆኛለሁ፤

ይህ ሁሉ ሀብት እያለኝ፣

ምንም ዐይነት በደል ወይም ኀጢአት አያገኙብኝም።”

9“ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ፣12፥9 ወይም በግብፅ ከነበራችሁበት ጊዜ አንሥቶ አምላካችሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤

በዓመት በዓላችሁ ቀን ታደርጉ እንደ ነበረው ሁሉ፣

እንደ ገና በድንኳኖች እንድትቀመጡ

አደርጋችኋለሁ።

10ለነቢያት ተናገርሁ፤

ራእይንም አበዛሁላቸው፤

በእነርሱም በኩል በምሳሌ ተናገርሁ።”

11ገለዓድ ክፉ ነው፤

ሕዝቡም ከንቱ ናቸው፤

ኮርማዎችን በጌልገላ ይሠዋሉን?

መሠዊያዎቻቸው በታረሰ መሬት ላይ እንዳለ፣

የድንጋይ ክምር ይሆናሉ።

12ያዕቆብ ወደ ሶርያ12፥12 ሰሜን መስጴጦምያን ያመለክታል ሸሸ፤

እስራኤል ሚስት ለማግኘት ሲል አገለገለ፤

ዋጋዋንም ለመክፈል በጎችን ጠበቀ።

13እግዚአብሔር በነቢይ አማካይነት እስራኤልን ከግብፅ አወጣ፤

በነቢይም በኩል ተንከባከበው።

14ኤፍሬም ግን ክፉኛ አስቈጣው፤

ጌታውም የደም አፍሳሽነቱን በደል በላዩ ላይ ያደርግበታል፤

ስለ ንቀቱም የሚገባውን ይከፍለዋል።

Japanese Contemporary Bible

ホセア書 12:1-14

12

1イスラエルは風を追い、

つむじ風の番をしています。

全く危険な遊びです。

エジプトやアッシリヤに贈り物をし、援助を求めますが、そのお返しは価値のない約束です。

2けれども、主はユダを告訴しようとしています。

ヤコブはその行いのゆえに、公正に罰せられます。

3ヤコブは生まれる時に兄弟と争い、

大人になってからは神とさえ戦ったのです。

4まさに、御使いと格闘して勝ちました。

彼は御使いに、祝福してくれるようにと

泣いて頼みました。

ベテルでは、

神と顔と顔を合わせるようにして出会い、

神は彼に語りかけました。

5まことに、主は天の軍勢の神であり、

主と呼ばれるにふさわしい方です。

6さあ、神に立ち返り、

愛と公正の原理に立ちなさい。

いつも、あなたの神に期待しなさい。

7ところが私の同胞は、不正なはかりで物を売る、

ずる賢い商人のようです。

だますことが好きなのです。

8エフライムは自慢しています。

「私はこんなに金持ちになった。

すべて自分でもうけたのだ。」

しかし、富に罪を償うことはできません。

9「わたしは、あなたをエジプトの奴隷生活から

救い出した主、同じ神だ。

わたしは、毎年の仮庵の祭りの時のように、

あなたを再び天幕(テント)に住まわせる。

10わたしは預言者を遣わし、

多くの幻やたとえや夢で警告した。」

11それなのに、ギルガルの罪は相も変わらず、

公然と行われています。

畑のうねのように何列も祭壇が築かれ、

偶像へのいけにえのために使われています。

ギルアデも、偶像を拝む愚か者であふれています。

12ヤコブはアラム(シリヤ)へ逃げ、

羊の番をして妻をめとりました。

13それから主はその民をエジプトから連れ出すために

一人の預言者を立て、

彼らを導き、守るようにさせました。

14それなのに、エフライムは主をひどく怒らせました。

その罪の支払いとして、主は死の宣告を下すのです。