Psalms 99 – NIV & NASV

New International Version

Psalms 99:1-9

Psalm 99

1The Lord reigns,

let the nations tremble;

he sits enthroned between the cherubim,

let the earth shake.

2Great is the Lord in Zion;

he is exalted over all the nations.

3Let them praise your great and awesome name—

he is holy.

4The King is mighty, he loves justice—

you have established equity;

in Jacob you have done

what is just and right.

5Exalt the Lord our God

and worship at his footstool;

he is holy.

6Moses and Aaron were among his priests,

Samuel was among those who called on his name;

they called on the Lord

and he answered them.

7He spoke to them from the pillar of cloud;

they kept his statutes and the decrees he gave them.

8Lord our God,

you answered them;

you were to Israel a forgiving God,

though you punished their misdeeds.99:8 Or God, / an avenger of the wrongs done to them

9Exalt the Lord our God

and worship at his holy mountain,

for the Lord our God is holy.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 99:1-9

መዝሙር 99

ጻድቅና ቅዱስ አምላክ

1እግዚአብሔር ነገሠ፤

ሕዝቦች ይንቀጥቀጡ፤

በኪሩቤል ላይ በዙፋን ተቀምጧል፤

ምድር ትናወጥ።

2እግዚአብሔር በጽዮን ታላቅ ነው፤

ከሕዝቦችም ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ብሏል።

3ታላቁንና አስፈሪውን ስምህን ይወድሱ፤

እርሱ ቅዱስ ነው።

4ፍትሕን የምትወድድ፣ ኀያል ንጉሥ ሆይ፤

አንተ ትክክለኝነትን መሠረትህ፤

ፍትሕንና ቅንነትንም፣

ለያዕቆብ አደረግህ።

5አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤

በእግሩ መርገጫ ስገዱ፤

እርሱ ቅዱስ ነውና።

6ሙሴና አሮን ካህናቱ ከሆኑት መካከል ነበሩ፤

ሳሙኤልም ስሙን ከጠሩት መካከል አንዱ ነበረ፤

እነርሱ ወደ እግዚአብሔር ተጣሩ፤

እርሱም መለሰላቸው።

7ከደመና ዐምድ ውስጥ ተናገራቸው፤

እነርሱም ሥርዐቱንና የሰጣቸውን ድንጋጌ ጠበቁ።

8እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤

አንተ መለስህላቸው፤

ጥፋታቸውን99፥8 ወይም የተፈጸመባቸውን በደል ማለት ነው። ብትበቀልም እንኳ፣

አንተ ይቅር የምትላቸው አምላክ ነህ።

9አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤

በቅዱስ ተራራውም ላይ ስገዱ፤

አምላካችን እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና።