Psalms 130 – NIV & NASV

New International Version

Psalms 130:1-8

Psalm 130

A song of ascents.

1Out of the depths I cry to you, Lord;

2Lord, hear my voice.

Let your ears be attentive

to my cry for mercy.

3If you, Lord, kept a record of sins,

Lord, who could stand?

4But with you there is forgiveness,

so that we can, with reverence, serve you.

5I wait for the Lord, my whole being waits,

and in his word I put my hope.

6I wait for the Lord

more than watchmen wait for the morning,

more than watchmen wait for the morning.

7Israel, put your hope in the Lord,

for with the Lord is unfailing love

and with him is full redemption.

8He himself will redeem Israel

from all their sins.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 130:1-8

መዝሙር 130

ለርዳታ የቀረበ ጥሪ

መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጥልቅ ወደ አንተ እጮኻለሁ።

2ጌታ ሆይ፤ ድምፄን ስማ፤

ጆሮዎችህ የልመናዬን ቃል፣

የሚያዳምጡ ይሁኑ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአትን ብትቈጣጠር፣

ጌታ ሆይ፤ ማን ሊቆም ይችላል?

4ነገር ግን በአንተ ዘንድ ይቅርታ አለ፤

ስለዚህም ልትፈራ ይገባሃል።

5እግዚአብሔርን ደጅ እጠናለሁ፤ ነፍሴም በትዕግሥት ትጠብቀዋለች፤

በቃሉም ተስፋ አደርጋለሁ።

6ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣

አዎን፤ ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣

ነፍሴ ጌታን ትጠባበቃለች።

7በእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረት፣

በእርሱም ዘንድ ማዳን አለና፣

እስራኤል ሆይ፤ በእግዚአብሔር ተስፋ አድርግ።

8እርሱም እስራኤልን፣

ከኀጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።