詩篇 8 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

詩篇 8:1-9

8

1ああ私たちの主よ。

御名の威厳と栄光は全地に満ち、

天にみなぎっています。

2あなたは幼子たちに、

あなたを真心からほめたたえよと教えられました。

その子どもたちの姿に、

敵が恥じ入って、口をつぐみますように。

3夜空を仰いで、

あなたが造られた月や星を眺めると、

4なぜ、取るに足りないちっぽけな人間を

心に留め、目をかけてくださるのか不思議です。

5ところがあなたは、

御使いにほんの少し及ばないだけの者として

人を造り、栄光と誉れの冠を与えられました。

6あなたは、お造りになった万物を、

人の手にゆだねられ、

いっさいのものは人の支配下にあります。

7牛も羊も、また野獣も、

8鳥、魚、すべての海の生物も。

9私たちの主よ。

御名の威厳と栄光は全地に満ちています。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 8:1-9

መዝሙር 8

የፈጣሪ ግርማ በፍጥረቱ ላይ

ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዜም፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤

ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ግርማዊ ነው!

ክብርህ ከሰማያት በላይ፣

ከፍ ከፍ ብሏል።

2ከልጆችና ጡት ከሚጠቡ ሕፃናት አፍ፣

ምስጋናን8፥2 ወይም ብርታትን አዘጋጀህ፤

ከጠላትህ የተነሣ፣

ባላንጣንና ቂመኛን ጸጥ ታሰኝ ዘንድ።

3የጣቶችህን ሥራ፣

ሰማያትህን ስመለከት፣

በስፍራቸው ያኖርሃቸውን፣

ጨረቃንና ከዋክብትን ሳይ፣

4በዐሳብህ ስፍራ ትሰጠው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

ትጠነቀቅለትም ዘንድ የሰው ልጅ ምንድን ነው?

5ከመላእክት በጥቂት አሳነስኸው፤

የክብርንና የሞገስን ዘውድ አቀዳጀኸው።

6በእጆችህ ሥራ ላይ ሾምኸው፤

ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛህለት፤

7በጎችንና ላሞችን ሁሉ፣

የዱር አራዊትንም፣

8የሰማይ ወፎችንና

የባሕር ዓሦችን፣

በባሕር ውስጥ የሚርመሰመሱትንም ሁሉ አስገዛህለት።

9እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤

ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ግርማዊ ነው!