ゼパニヤ書 1 – JCB & NASV

Japanese Contemporary Bible

ゼパニヤ書 1:1-18

1

1表題――主からのことば。あて先――ゼパニヤ。彼はクシの子、ゲダルヤの孫、アマルヤの曾孫、ヒゼキヤの曾々孫。時代――ユダの王、アモンの子ヨシヤの治世。

主の日に下される全世界へのさばき

2主はこう言う。

「わたしは、おまえの国にあるものを一掃し、

徹底的に滅ぼす。

3人も動物もだ。

人間と人間が拝む偶像、すべては消え去る。

空の鳥も海の魚も死に絶える。

4わたしはこぶしでユダとエルサレムを打ち砕き、

残っているバアルの礼拝者を断ち滅ぼす。

偶像に仕える祭司を抹殺し、

そのため、彼らの記憶さえ消え去る。

5彼らは屋上に上って、太陽や月や星を拝んでいる。

『主に従っている』と言いながら、

モレクをも礼拝している。

わたしは、そんな彼らを滅ぼす。

6そして、以前は主を礼拝していたのに

今は礼拝していない者や、主を愛したことも

愛そうと思ったこともない者を滅ぼす。」

7静まって、主の前に立て。

主のさばきの恐ろしい日がくるからだ。

神はご自分の民を虐殺する手はずを整え、

死刑執行人を選んでいる。

8「さばきの日に、わたしはユダの指導者と君主たち、

それに異教の服を着ている者すべてを罰する。

9そうだ、異教の習慣に従う者や、

盗みや人殺しをほしいままにして、

主人の家を暴力と詐欺による邪悪な利得で満たす者を

罰する。

10警告を発する叫び声が、

エルサレムの中心から遠く離れた門から上がり、

だんだん近づいてきて、ついに前進する軍勢の音が、

町が立っている丘の頂に達する。

11エルサレムの民よ、泣き悲しめ。

町の貪欲な商売人、高利貸しは一人残らず死ぬのだ。

12わたしは、ともしびをかざして、

エルサレムの暗い隅々まで捜し回る。

罪にどっぷりつかり、神に関心を示さず、

神はそっとしておいてくれると考えている者たちを

見つけ出して罰するのだ。

13彼らの財産は敵に奪われ、家は荒らされる。

自分たちが建てた新しい家に住む機会は決してない。

自分たちが植えたぶどう畑のぶどう酒を

飲むことも決してない。

14その恐るべき日は近い。

急ぎ足でやってくる。

その日には、勇士たちも泣きくずれる。

15それは神の怒りが注ぎ出される日、

恐ろしい苦悩と苦痛の日、崩壊と荒廃の日、

暗闇と陰鬱、

暗雲と暗黒の日。

16角笛が吹き鳴らされ、ときの声が上がる。

城壁で囲まれた町と、最も強固な胸壁が崩れ落ちる。

17わたしは彼らを、

目が見えずに手探りで道を捜し回る人のように

無力にする。主に罪を犯したからだ。

それで、彼らの血はちりの中に注ぎ出され、

死体は地面に置かれたまま朽ちはてる。」

18あなたがたの金銀も、主の怒りの日には役に立たない。

そんなもので自分の身代金を払うことはできない。

神のねたみの炎が、全地をなめ尽くすからだ。

神はユダの民すべてをたちまちのうちに取り除く。

New Amharic Standard Version

ሶፎንያስ 1:1-18

1በይሁዳ ንጉሥ በአሞጽ ልጅ በኢዮስያስ ዘመን ወደ ሕዝቅያስ ልጅ፣ ወደ አማርያ ልጅ፣ ወደ ጎዶልያስ ልጅ፣ ወደ ኵሲ ልጅ ወደ ሶፎንያስ የመጣ የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

ስለሚመጣው ጥፋት የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

2“ማንኛውንም ነገር፣

ከምድር ገጽ አጠፋለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

3“ሰውንና እንስሳን አጠፋለሁ፤

የሰማይን ወፎች፣

የባሕርንም ዓሦች አጠፋለሁ፤

ሰውን ከምድር ገጽ በማስወግድበት ጊዜ፣

ክፉዎች የፍርስራሽ1፥3 የዕብራይስጡ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ክምር ይሆናሉ”

ይላል እግዚአብሔር

በይሁዳ ላይ የተነገረ ጥፋት

4“እጄን በይሁዳ፣

በኢየሩሳሌምም በሚኖሩት ሁሉ ላይ አነሣለሁ፤

የበኣልን ትሩፍ፣

የጣዖታቱንና የአመንዝራ ካህናቱን ስም ሁሉ ከዚህ ስፍራ አጠፋለሁ፤

5የሰማይን ሰራዊት ለማምለክ፣

በሰገነት ላይ ወጥተው የሚሰግዱትን፣

ለእግዚአብሔር እየሰገዱ፣ በስሙም እየማሉ፣

በሚልኮምም1፥5 በዕብራይስጥ ማልካም ይባላል። ደግሞ የሚምሉትን፣

6እግዚአብሔርን ከመከተል ወደ ኋላ የሚመለሱትን፣

እግዚአብሔርን የማይፈልጉትን፣ እንዲረዳቸውም የማይጠይቁትን አጠፋለሁ።”

7በጌታ እግዚአብሔር ፊት ዝም በሉ፤

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና።

እግዚአብሔር መሥዋዕት አዘጋጅቷል፤

የጠራቸውንም ቀድሷል።

8በእግዚአብሔር የመሥዋዕት ቀን፣

መሳፍንቱንና የንጉሡን ልጆች፣

እንግዳ ልብስ የሚለብሱትን ሁሉ እቀጣለሁ።

9በዚያን ቀን፣

በመድረኩ ላይ የሚዘልሉትን ሁሉ፣

የአማልክታቸውን ቤት፣

በዐመፅና በማጭበርበር የሚሞሉትን እቀጣለሁ።

10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በዚያ ቀን ‘ከዓሣ በር’ ጩኸት

በሁለተኛው አደባባይ ዋይታ፣

ከኰረብቶችም ታላቅ ሽብር ይሰማል።

11እናንት በመክቴሽ1፥11 አንዳንዶች በሞርታር ይላሉ። ገበያ የምትኖሩ ዋይ በሉ፤

ነጋዴዎቻችሁ ሁሉ ይደመሰሳሉ፤

በብር የሚነግዱትም ሁሉ ይሞታሉ።

12በዚያ ዘመን ኢየሩሳሌምን በመብራት እፈትሻለሁ፤

ተንደላቅቀው የሚኖሩትን፣

በዝቃጩ ላይ እንደ ቀረ የወይን ጠጅ የሆኑትን፣

‘ክፉም ይሁን መልካም፣

እግዚአብሔር ምንም አያደርግም’ የሚሉትን ቸልተኞች እቀጣለሁ።

13ሀብታቸው ይዘረፋል፤

ቤታቸው ይፈራርሳል፤

ቤቶች ይሠራሉ፤

ነገር ግን አይኖሩባቸውም፤

ወይን ይተክላሉ፤

ጠጁን ግን አይጠጡም።”

ታላቁ የእግዚአብሔር ቀን

14“ታላቁ የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው፤

ቅርብ ነው ፈጥኖም ይመጣል፤

በእግዚአብሔር ቀን የሚሰማው ልቅሶ መራራ ነው፤

በዚያ ጦረኛውም ምርር ብሎ ይጮኻል፤

15ያ ቀን የመዓት ቀን፣

የመከራና የጭንቀት ቀን፣

የሁከትና የጥፋት ቀን፣

የጨለማና የጭጋግ ቀን፣

የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን ይሆናል፤

16ያ ቀን በተመሸጉ ከተሞችና፣

በረዣዥም ግንቦች ላይ፣

የመለከት ድምፅና የጦርነት ጩኸት የሚሰማበት ቀን ይሆናል።

17“እንደ ዕውር እንዲራመዱ፣

በሰዎች ላይ ጭንቀት አመጣባቸዋለሁ፤

በእግዚአብሔር ላይ ኀጢአትን ሠርተዋልና።

ደማቸው እንደ ትቢያ፣

ሥጋቸውም እንደ ጕድፍ ይጣላል።

18በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን፣

ብራቸውም ሆነ ወርቃቸው

ሊያድናቸው አይችልም።”

መላዪቱ ምድር፣

በቅናቱ ትበላለች፤

በምድር በሚኖሩ ሁሉ ላይ፣

ድንገተኛ ፍጻሜ ያመጣባቸዋልና።