Psalmen 20 – HTB & NASV

Het Boek

Psalmen 20:1-9

1Voor muziekbegeleiding. Een psalm van David. Moge Jahweh op de dag van nood u verhoren, De naam van Jakobs God u beschermen, 2Uit het heiligdom u hulp verlenen, En uit Sion u bijstaan. 3Hij gedenke al uw offergaven, En neme genadig uw brandoffers aan; 4Hij schenke u wat uw hart maar begeert, En doe al uw plannen gelukken. 5Dan zullen wij om uw zegepraal juichen, In de Naam van onzen God de feestbanier heffen! 6Nu reeds ben ik er zeker van, Dat Jahweh zijn Gezalfde de zegepraal schenkt, En Hem uit zijn heilige hemel verhoort Door de reddende kracht van zijn rechterhand. 7Anderen gaan trots op wagens en paarden, Wij op de Naam van Jahweh, onzen God; 8Maar zìj storten neer, en blijven liggen, Wij rijzen op en staan vast! 9Jahweh, geef den Koning de zege, En verhoor nog heden ons smeekgebed!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 20:1-9

መዝሙር 20

ጸሎት ለንጉሡ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር በጭንቅ ቀን ይስማህ፤

የያዕቆብም አምላክ ስም ይጠብቅህ።

2ከመቅደሱ ረድኤት ይላክልህ፤

ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ።

3ቍርባንህን ሁሉ ያስብልህ፤

የሚቃጠል መሥዋዕትህን ይቀበልልህ። ሴላ

4የልብህን መሻት ይስጥህ፤

ዕቅድህን ሁሉ ያከናውንልህ።

5በአንተ ድል ደስ ይበለን፤

በአምላካችን ስም አርማችንን ከፍ እናደርጋለን፤

እግዚአብሔር የለመንኸውን ሁሉ ይፈጽምልህ።

6እግዚአብሔር፣ የቀባውን እንደሚያድን

አሁን ዐወቅሁ፤

የማዳን ኀይል ባለው ቀኝ እጁ፣

ከተቀደሰው ሰማይ ይመልስለታል።

7እነዚህ በሰረገላ፣ እነዚያ በፈረስ ይመካሉ፤

እኛ ግን ትምክሕታችን የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም ነው።

8እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ፤

እኛ ግን ተነሣን፤ ጸንተንም ቆምን።

9እግዚአብሔር ሆይ፤ ንጉሥን አድን፤

እኛም በጠራንህ ቀን ስማን።20፥9 ወይም አድን! ንጉሥ ሆይ፤ ስማን