התגלות 10 – HHH & NASV

Habrit Hakhadasha/Haderekh

התגלות 10:1-11

1לאחר מכן ראיתי מלאך גיבור אחר יורד מן השמים. הוא היה עטוף בענן, ומעל ראשו מעין קשת; פניו זרחו כשמש, רגליו דמו לעמודי אש 2ובידו החזיק ספר קטן פתוח. רגלו הימנית דרכה על הארץ, 3והוא קרא קריאה אדירה כשאגת אריה. בתגובה לקריאתו הרימו שבעת הרעמים את קולם והחלו לדבר.

4בשעה שדיברו שבעת הרעמים רציתי לכתוב את דבריהם, אך שמעתי קול מן השמים שציווה עלי: ”דברי הרעמים הם סוד. אל תעלה אותם על הנייר!“

5המלאך הגיבור, שראיתיו עומד על הים ועל הארץ, הרים את יד ימינו כלפי השמים 6ונשבע בשמו של החי לנצח, האלוהים אשר ברא את השמים, הארץ, הים ואת כל אשר בהם: ”לא יהיה עיכוב נוסף! 7בימי תקיעת המלאך השביעי בשופרו, כאשר יחל לתקוע, יתגלה סודו של אלוהים, כפי שבישר לעבדיו הנביאים.“

8הקול אשר שמעתי מן השמים דיבר אלי שנית: ”לך, קח את הספר הקטן ופתוח מיד המלאך שעומד על הים ועל הארץ.“

9ניגשתי אליו וביקשתי ממנו את הספר. ”קח ואכול אותו“, אמר לי המלאך. ”בפיך יהיה טעמו כדבש, אך לאחר שתבלע אותו הוא יהיה מר בבטנך!“

10לקחתי את הספר מהמלאך ואכלתי אותו. בפי היה טעמו כדבש, אך לאחר שבלעתי אותו כאבה בטני וחשתי במרירות.

11”עליך לשוב ולנבא על ארצות, עמים, שבטים, שפות ומלכים רבים“, אמר אלי המלאך.

New Amharic Standard Version

ራእይ 10:1-11

መልአኩና ትንሿ መጽሐፍ

1ከዚህ በኋላ ሌላ ብርቱ መልአክ ደመና ተጐናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ እርሱም በራሱ ላይ ቀስተ ደመና ነበር። ፊቱ እንደ ፀሓይ፣ እግሮቹ እንደ እሳት ዐምዶች ነበሩ። 2በእጁም የተከፈተች ትንሽ ጥቅልል መጽሐፍ ይዞ ነበር፤ ቀኝ እግሩን በባሕር ላይ፣ ግራ እግሩን በምድር ላይ አኖረ፤ 3እንደሚያገሣ አንበሳም ድምፁን ከፍ አድርጎ ጮኸ፤ በጮኸም ጊዜ የሰባቱ ነጐድጓዶች ድምፆች ተናገሩ። 4ሰባቱ ነጐድጓዶች በተናገሩ ጊዜ፣ ለመጻፍ ተዘጋጀሁ፤ ነገር ግን፣ “ሰባቱ ነጐድጓዶች የተናገሩትን በማኅተም ዝጋው እንጂ አትጻፍ” የሚል ድምፅ ከሰማይ ሰማሁ።

5ከዚህ በኋላ በባሕርና በምድር ላይ ቆሞ ያየሁት መልአክ ቀኝ እጁን ወደ ሰማይ አነሣ፤ 6እርሱም ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው፣ ሰማይንና በውስጡ ያሉትን፣ ምድርንና በውስጧ ያሉትን፣ ባሕርንና በውስጡ ያሉትን በፈጠረው በእርሱ ማለ፤ እንዲህም አለ፤ “ከእንግዲህ መዘግየት አይኖርም፤ 7ነገር ግን ሰባተኛው መልአክ መለከቱን በሚነፋባቸው ቀኖች፣ ለአገልጋዮቹ ለነቢያት በገለጠላቸው መሠረት የእግዚአብሔር ምስጢር ይፈጸማል።”

8ከዚያም ከሰማይ የሰማሁት ድምፅ እንደ ገና እንዲህ ሲል ተናገረ፤ “ሂድ፤ በባሕርና በምድር ላይ ከቆመው መልአክ እጅ የተከፈተችውን ጥቅልል መጽሐፍ ውሰድ።”

9እኔም ወደ መልአኩ ሄጄ ትንሿን ጥቅልል መጽሐፍ እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፤ እርሱም፣ “ውሰድና ብላት፤ ሆድህን መራራ ታደርገዋለች፤ በአፍህ ግን እንደ ማር ትጣፍጣለች” አለኝ። 10ትንሿንም መጽሐፍ ከመልአኩ እጅ ተቀብዬ በላኋት፤ በአፌ እንደ ማር ጣፈጠች፤ ከበላኋት በኋላ ግን ሆዴ መራራ ሆነ፤ 11ከዚያም፣ “ስለ ብዙ ሕዝቦች፣ ወገኖች፣ ቋንቋዎችና ነገሥታት እንደ ገና ትንቢት ልትናገር ይገባሃል” ተባልሁ።