以色列人受欺壓
1以色列的眾子帶著家眷跟雅各1·1 「雅各」就是「以色列」,上帝為雅各改名以色列,故事參考創世記32·28。一起去了埃及,以下是他們的名字: 2呂便、西緬、利未、猶大、 3以薩迦、西布倫、便雅憫、 4但、拿弗他利、迦得、亞設。 5雅各的子孫總共有七十人。那時,約瑟已經住在埃及。 6後來,約瑟和他的弟兄以及同輩的人都相繼去世。 7以色列人生養眾多,人口大增,很快就遍佈埃及,成為一個強大的民族。 8那時,埃及有一位不認識約瑟的新王登基, 9對他的百姓說:「你們看,以色列人比我們多,又比我們強。 10來吧!我們要設法阻止他們人口增長,否則一遇到戰爭,他們便會加入我們敵人的陣營來攻打我們,然後一走了之。」
11於是,埃及人派監工強迫以色列人服勞役,在比東和蘭塞兩地為法老興建儲貨城。 12以色列人越受奴役,人口增長得越快,散居的範圍也越廣,令埃及人感到恐懼。 13於是,埃及人更殘酷地奴役他們, 14強迫他們和泥造磚,並做田間一切的苦工,使他們痛苦不堪。 15埃及王又命令兩個希伯來的接生婆施弗拉和普阿: 16「你們在替希伯來婦女接生的時候,如果看到生下的是男嬰,就把他殺掉;如果是女嬰,就讓她活下來。」 17但這兩個接生婆敬畏上帝,沒有執行王的命令,而是保留了男嬰的性命。 18埃及王召見那兩個接生婆,質問她們:「你們為什麼這樣做?為什麼讓男嬰活著?」 19她們回答說:「因為希伯來婦女跟埃及婦女不同。她們身體強健,我們還沒有趕到,嬰兒就生下來了。」 20-21因此,以色列人口繼續增加,更加繁盛。因為這兩個接生婆敬畏上帝,上帝便賜福給她們,使她們生兒育女。 22後來,法老命令全埃及的人把以色列人生的所有男嬰都拋進尼羅河裡,只讓女嬰活著。
እስራኤላውያን በጭቈና ሥር
1ቤተ ሰቦቻቸውን ይዘው ከያዕቆብ ጋር ወደ ግብፅ የሄዱት የእስራኤል ልጆች ስሞች እነዚህ ናቸው፦
2ሮቤል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣
3ይሳኮር፣ ዛብሎን፣ ብንያም፣
4ዳን፣ ንፍታሌም፣
ጋድና አሴር።
5የያዕቆብ ዘር ጠቅላላ ብዛት ሰባ1፥5 የማሶሬቱ ቅጅ (ዘፍ 46፥27 ይመ)፣ የሙት ባሕር ጥቅልል እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም (ሐሥ 7፥14 እና የዘፍ 46፥27 ማብ ይመ)፣ ሰባ አምስት ይላሉ። ሲሆን፣ ዮሴፍ ግን ቀደም ብሎ በግብፅ ነበረ።
6ከጊዜ በኋላ ዮሴፍና ወንድሞቹ ያም ትውልድ በሙሉ ሞቱ፤ 7ይሁን እንጂ እስራኤላውያን እየተዋለዱ በዙ፤ ቍጥራቸው እጅግ ከመጨመሩም የተነሣ የግብፅን ምድር ሞሏት።
8በግብፅም፣ ስለ ዮሴፍ የማያውቅ አዲስ ንጉሥ ነገሠ። 9እርሱም ሕዝቡን እንዲህ አላቸው፤ “እነሆ፤ እስራኤላውያን በቍጥር በልጠውናል፤ ከእኛም ይልቅ እየበረቱ ነው፤ 10ቍጥራቸው እንዳይጨምር፣ ጦርነት ቢነሣ ከጠላቶቻችን ጋር አብረው እንዳይወጉንና ከምድሪቱም ኰብልለው እንዳይሄዱ ዘዴ እንፈልግ።”
11ስለዚህ እያስጨነቁ የግዳጅ ሥራ የሚያሠሯቸውን አሠሪ አለቆች ሾሙባቸው። እስራኤላውያንም ፊቶምና ራምሴ የተባሉ ንብረት ማከማቻ ከተሞችን ለፈርዖን ሠሩለት። 12ነገር ግን ባስጨነቋቸው መጠን የእስራኤላውያን ቍጥር በዛ፤ በምድሪቱም እየተስፋፉ ሄዱ፤ ከዚህም የተነሣ ግብፃውያኑ እስራኤላውያንን እጅግ ፈሯቸው፤ 13ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታም ያሠሯቸው ጀመር። 14ጭቃ በማስቦካት፣ ጡብ በማሠራትና በእርሻም ሁሉ እያስጨነቁ ከባድ ሥራ እንዲሠሩ በማድረግ ሕይወታቸውን አስመረሩ፤ ግብፃውያኑ በሚያሠሯቸው ከባድ ሥራ ሁሉ ፈጽሞ አይራሩላቸውም ነበር።
15የግብፅም ንጉሥ ሲፓራና ፉሐ የተባሉትን ዕብራውያን ሴቶች አዋላጆች እንዲህ አላቸው፤ 16“የዕብራውያንን ሴቶች በማማጫው ድንጋይ ላይ በምታዋልዱበት ጊዜ የሚወለደው ሕፃን ወንድ ከሆነ ግደሉት፤ ሴት ከሆነች ግን በሕይወት ትኑር።” 17አዋላጆቹ ግን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ስለ ፈሩ የግብፅ ንጉሥ ያዘዛቸውን አልፈጸሙም፤ ወንዶቹንም ልጆች በሕይወት እንዲኖሩ ተዉአቸው። 18ንጉሡም አዋላጆቹን ጠርቶ፣ “ለምንድን ነው ወንዶቹን ልጆች በሕይወት እንዲኖሩ የተዋችኋቸው?” አላቸው።
19እነርሱም፣ “የዕብራውያን ሴቶች እንደ ግብፃውያን ሴቶች አይደሉም፤ ብርቱዎች ስለሆኑ አዋላጆች ከመድረሳቸው በፊት ይወልዳሉ” ሲሉ ለፈርዖን መለሱለት።
20ከዚህም የተነሣ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ለአዋላጆቹ መልካም ሆነላቸው፤ ሕዝቡም በቍጥር እየበዛና እያየለ ሄደ። 21አዋላጆቹም እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) በመፍራታቸው ቤተ ሰብ ሰጣቸው።
22ፈርዖንም፣ “የሚወለደውን ወንድ ልጅ1፥22 የማሶሬቱ ቅጅ፣ ኦሪተ ሳምራውያን፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም እንዲሁም ታርጕም ከዕብራውያን የሚወለደውን ይላሉ። ሁሉ አባይ ወንዝ ውስጥ ጣሉት፤ ሴት ልጅ ሁሉ ግን በሕይወት ትኑር” ሲል ሕዝቡን አዘዘ።