诗篇 130 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 130:1-8

第 130 篇

患难中求助的祷告

上圣殿朝圣之诗。

1耶和华啊!

我在绝望的深渊中向你呼求。

2主啊,求你垂听我的呼求,

侧耳听我的祈求。

3主耶和华啊,

倘若你追究我们的罪过,

谁能站得住呢?

4然而,你赦免我们,

所以你当受敬畏。

5我等候耶和华,一心等候祂,

祂的话语是我的盼望。

6我一心等候耶和华,

比守夜的盼望天明还要迫切,

比守夜的盼望天明还要迫切。

7以色列啊,要信靠耶和华,

因为祂有慈爱,能完全救赎我们。

8祂必把以色列从罪恶中救赎出来。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 130:1-8

መዝሙር 130

ለርዳታ የቀረበ ጥሪ

መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጥልቅ ወደ አንተ እጮኻለሁ።

2ጌታ ሆይ፤ ድምፄን ስማ፤

ጆሮዎችህ የልመናዬን ቃል፣

የሚያዳምጡ ይሁኑ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአትን ብትቈጣጠር፣

ጌታ ሆይ፤ ማን ሊቆም ይችላል?

4ነገር ግን በአንተ ዘንድ ይቅርታ አለ፤

ስለዚህም ልትፈራ ይገባሃል።

5እግዚአብሔርን ደጅ እጠናለሁ፤ ነፍሴም በትዕግሥት ትጠብቀዋለች፤

በቃሉም ተስፋ አደርጋለሁ።

6ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣

አዎን፤ ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣

ነፍሴ ጌታን ትጠባበቃለች።

7በእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረት፣

በእርሱም ዘንድ ማዳን አለና፣

እስራኤል ሆይ፤ በእግዚአብሔር ተስፋ አድርግ።

8እርሱም እስራኤልን፣

ከኀጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።