撒母耳记上 11 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒母耳记上 11:1-15

扫罗打败亚扪人

1亚扪拿辖率军上来围困基列·雅比,城内的居民对拿辖说:“你与我们立约吧!我们愿意服从你。” 2亚扪拿辖说:“好,但有一个条件,我要挖去你们每一个人的右眼作为对全体以色列人的羞辱。” 3雅比的长老说:“请宽限我们七天,我们好派遣使者去以色列全境。要是没有人来营救我们,我们就向你投降。” 4雅比的使者来到扫罗的家乡基比亚,把他们的情况告诉众人,大家听了放声大哭。 5那时扫罗刚好赶着牛从田间回来,便问道:“发生了什么事?为什么大家都在哭?”百姓把雅比的情况告诉了他。 6扫罗听后,上帝的灵降在他身上,他勃然大怒, 7牵来两头牛,把它们切成碎块,然后派使者把碎块分发到以色列全境,并且宣布:“谁拒绝跟随扫罗撒母耳出战,他的牛就要被砍成这样。”上帝使百姓充满恐惧,他们都同心合意地响应。 8扫罗比色统计以色列人,共有三十万,从犹大来的有三万。 9他们让雅比的使者回去告诉基列·雅比人,说:“明天中午,你们必得拯救。”使者回去告诉雅比人,他们非常欢喜, 10便对亚扪人说:“明天我们会出来归顺你们,你们怎样对待我们都可以。” 11第二天,扫罗以色列人分成三队,在黎明时分突袭亚扪人的军营,把他们杀得大败,直到中午才收兵。亚扪人的残兵四散奔逃。

12以色列人对撒母耳说:“是谁说扫罗不该做王?把他们带来,我们要处死他们。” 13扫罗却说:“今天不可杀人,因为今天耶和华拯救了以色列。” 14撒母耳对民众说:“来吧,我们到吉甲去,在那里重新立国。” 15于是,他们来到吉甲,在耶和华面前立扫罗为王,又向耶和华献上平安祭。扫罗和全体以色列人都非常欢喜。

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 11:1-15

ሳኦል የኢያቢስን ከተማ ታደገ

1አሞናዊው ናዖስ ወጥቶ ኢያቢስ ገለዓድን ከበባት፤ የኢያቢስም ሰዎች ሁሉ፣ “ከእኛ ጋር ቃል ኪዳን አድርግ፣ እኛም እንገዛልሃለን” አሉት።

2አሞናዊው ናዖስ፣ “ከእናንተ ጋር ቃል ኪዳን የማደርገው የእያንዳንዳችሁን ቀኝ ዐይን አውጥቼ እስራኤልን ሁሉ ካዋረድሁ በኋላ ብቻ ነው” ሲል መለሰ።

3የኢያቢስም ሽማግሌዎች፣ “ወደ መላው እስራኤል መልእክተኞችን እንድንልክ የሰባት ቀን ጊዜ ስጠን፤ ሊታደገን የሚመጣ ሰው ከሌለ፣ ለአንተ እንገዛለን” አሉት።

4መልእክተኞቹም ሳኦል ወዳለበት ወደ ጊብዓ መጥተው ይህን ለሕዝቡ በተናገሩ ጊዜ፣ ሕዝቡ ሁሉ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው አለቀሱ፤ 5በዚህ ጊዜ፣ ሳኦል በሬዎቹን እየነዳ ከዕርሻ ተመለሰ፤ እርሱም፣ “ሕዝቡ የሚያለቅሰው ምን ሆኖ ነው?” ሲል ጠየቀ። እነርሱም የኢያቢስ ሰዎች ያሏቸውን ነገሩት።

6ሳኦል ይህን በሰማ ጊዜ የእግዚአብሔር መንፈስ በኀይል ወረደበት፤ እጅግ ተቈጣ። 7ጥንድ በሬዎች ወስዶ ቈራረጠ፤ ሥጋቸውንም በመልእክተኞች እጅ ልኮ፣ “ሳኦልንና ሳሙኤልን የማይከተል ሰው በሬው እንደዚህ ይቈራረጣል” ሲል በመላው እስራኤል አስነገረ። ታላቅ ፍርሀት ከእግዚአብሔር ዘንድ በሕዝቡ ላይ ወደቀ፤ ሕዝቡም እንደ አንድ ሰው ሆኖ ወጣ። 8ሳኦል ቤዜቅ በተባለ ስፍራ ሰራዊቱን በሰበሰበ ጊዜ፤ ቍጥራቸው ከእስራኤል ሦስት መቶ ሺሕ፣ ከይሁዳም ሠላሳ ሺሕ ነበር።

9ከዚያ ለመጡትም መልእክተኞች፣ “ለኢያቢስ ገለዓድ ሰዎች፣ ‘ነገ ፀሓይ ሞቅ በሚልበት ጊዜ ነጻ ትሆናላችሁ’ ብላችሁ ንገሯቸው” አሏቸው። መልእክተኞቹም ሄደው ለኢያቢስ ሰዎች ይህንኑ በነገሯቸው ጊዜ በደስታ ፈነደቁ። 10ለአሞናውያንም፣ “እኛ ነገ እጃችንን እንሰጣችኋለን፤ እናንተም መልካም መስሎ የታያችሁን ሁሉ ልታደርጉብን ትችላላችሁ” አሏቸው።

11በማግስቱም ሳኦል ሰራዊቱን ከሦስት ቦታ ከፈለው፤ ሊነጋጋ ሲል፣ የአሞናውያንን ሰፈር ጥሰው በመግባት ፀሓይ ሞቅ እስኪል ድረስ ፈጇቸው። በሕይወት የተረፉትም ሁለት እንኳ ሆነው በአንድ ላይ ሊሆኑ እስከማይችሉ ድረስ ተበታተኑ።

የሳኦል ንጉሥነት ተረጋገጠ

12ሕዝቡ ሳሙኤልን፣ “ ‘ሳኦል እንዴት ሊገዛን ይችላል!’ ያሉት እነማን ነበሩ? እነዚህን ሰዎች እንገድላቸው ዘንድ አምጣቸው” አሉት።

13ሳኦል ግን፣ “ይህ ዕለት እግዚአብሔር እስራኤልን የታደገበት ቀን ስለሆነ፣ በዛሬው ዕለት ማንም ሰው አይገደልም” አለ።

14ከዚያም ሳሙኤል ሕዝቡን፣ “ኑና ወደ ጌልገላ እንሂድ፤ ንግሥናውን እናጽና” አለ። 15ሕዝቡ ሁሉ ወደ ጌልገላ ሄደ፤ የሳኦልንም ንጉሥነት በእግዚአብሔር ፊት አጸና። በዚያም ሕዝቡ የኅብረት መሥዋዕት11፥15 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። በእግዚአብሔር ፊት አቀረበ፤ ሳኦልና እስራኤላውያንም ሁሉ ታላቅ በዓል አደረጉ።