尼希米记 1 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

尼希米记 1:1-11

尼希米的祷告

1以下是哈迦利亚的儿子尼希米的记述。

波斯亚达薛西二十年基斯流月1:1 基斯流月”即希伯来历的九月,阳历是十一月中旬到十二月中旬。,我在书珊城里。 2犹大来了我的一个兄弟哈拿尼和一些人,我问他们有关从流亡之地归回的犹太余民和耶路撒冷的情况。 3他们回答说:“那些从流亡之地归回犹大省的人深陷苦难,饱受凌辱。耶路撒冷的城墙已经倒塌,城门也被烧毁。”

4我一听见这消息,就坐下痛哭,悲伤了好几天。我在天上的上帝面前禁食祷告,说:

5“天上的上帝耶和华啊,你是伟大而可畏的上帝,你向爱你、守你诫命的人守约,施慈爱。 6仆人在你面前昼夜为你的众仆人以色列民祈祷,求你睁眼察看,侧耳倾听。我承认以色列人向你所犯的罪,以及我和我的家族所犯的罪。 7我们行事败坏,没有遵守你赐给你仆人摩西的诫命、律例和典章。 8求你顾念你对你仆人摩西所说的话,‘如果你们不忠,我必把你们驱散到列邦中。 9但如果你们转向我,谨遵我的诫命,即使你们流落天涯,我也必从那里把你们召集到我选为我名所在之地。’ 10我们是你的仆人、你的子民,是你用大能大力救赎的。 11主啊,求你侧耳听你仆人的祷告,垂听那些喜爱敬畏你名的众仆人的祈求,使你仆人今天亨通,在王面前蒙恩。”

我是王的侍酒总管。

New Amharic Standard Version

ነህምያ 1:1-11

የነህምያ ጸሎት

1የሐካልያ ልጅ የነህምያ ቃል፤

በሃያኛው ዓመት ካሴሉ በተባለው ወር በሱሳ ግንብ ሳለሁ፣ 2ከወንድሞቼ አንዱ የሆነው አናኒ፣ ከሌሎች ጥቂት ሰዎች ጋር ከይሁዳ መጣ፤ እኔም ከምርኮ ስለ ተረፉት የአይሁድ ቅሬታዎችና ስለ ኢየሩሳሌም ጠየቅኋቸው።

3እነርሱም፣ “በሕይወት ተርፈው ከምርኮ ወደ አገራቸው የተመለሱት ሰዎች በታላቅ መከራና ውርደት ላይ ይገኛሉ፤ የኢየሩሳሌም ቅጥር ፈራርሷል፤ በሮቿም በእሳት ተቃጥለዋል” አሉኝ።

4ይህን ነገር በሰማሁ ጊዜ አያሌ ቀናት ዐዘንሁ፤ ጾምሁ፤ ጸለይሁም። 5ከዚያም እንዲህ አልሁ፤

“ለሚወድዱህና ትእዛዝህን ለሚያከብሩ የፍቅርህን ቃል ኪዳን የምትጠብቅ ታላቅና የተፈራህ አምላክ፣ የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ 6ባሪያህ ስለ አገልጋዮችህ ስለ እስራኤል ሕዝብ ቀንና ሌሊት በፊትህ የሚጸልየውን ጸሎት ለመስማት ጆሮህ ይንቃ፤ ዐይንህም ይከፈት። እኔንና የአባቴን ቤት ጨምሮ እኛ እስራኤላውያን አንተን በመበደል የሠራነውን ኀጢአት እናዘዛለሁ። 7በአንተ ላይ እጅግ ክፉ ሥራ ሠርተናል፤ ለባሪያህም ለሙሴ የሰጠኸውን ትእዛዝ፣ ሥርዐትና ሕግ አልጠበቅንም።

8“ለባሪያህ ለሙሴ እንዲህ ስትል የሰጠኸውን ቃል ዐስብ፤ ‘ታማኞች ካልሆናችሁ፣ በአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፤ 9ወደ እኔ ብትመለሱና ትእዛዞቼን ብትፈጽሙ፣ የተሰደዱት ወገኖቻችሁ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ እንኳ ቢበተኑ፣ ከዚያ እሰበስባቸዋለሁ፤ ለስሜም ማደሪያ ወደ መረጥሁት ስፍራ አመጣቸዋለሁ።’

10“እነዚህም በታላቁ ኀይልህና በብርቱ እጅህ የተቤዠሃቸው ባሪያዎችህና ሕዝብህ ናቸው። 11ጌታ ሆይ፤ የባሪያህን ጸሎት፣ ስምህን በመፍራት ደስ የሚሰኙትን የባሪያዎችህንም ጸሎት ጆሮህ ታድምጥ። በዚህ ሰው ፊት ሞገስን አድርገህለት ዛሬ ለባሪያህ መከናወንን ስጠው።”

በዚያን ጊዜ እኔ የንጉሡ ጠጅ አሳላፊ ነበርሁ።