创世记 12 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

创世记 12:1-20

上帝呼召亚伯兰

1耶和华对亚伯兰说:“你要离开家乡、亲族和父亲的家,到我要指示你的地方去。 2我必使你成为大国,我必赐福给你,使你声名远播。你必成为别人的祝福。 3我必赐福给那些祝福你的人,咒诅那些咒诅你的人。世上万族必因你而蒙福。”

4亚伯兰就照耶和华的吩咐离开哈兰,侄儿罗得与他同行。那时亚伯兰七十五岁。 5亚伯兰带着妻子撒莱、侄儿罗得以及在哈兰积攒的财物和所得的奴仆启程来到迦南。到了迦南以后, 6亚伯兰继续前行,来到示剑摩利橡树12:6 橡树”希伯来文是“大树”,也可能指灵树或圣树,下同13:1814:1318:135:435:8那里。当时迦南人住在那地方。 7耶和华向亚伯兰显现,对他说:“我要把这片土地赐给你的后裔。”亚伯兰就在那里为向他显现的耶和华筑了一座坛。 8然后,他们又启程前往伯特利东面的山区,在那里搭起帐篷。他们的西面是伯特利,东面是亚伯兰又在那里筑了一座坛,求告耶和华。 9之后,亚伯兰继续前往南地。

亚伯兰逃荒到埃及

10当时,那地方闹饥荒,灾情非常严重,亚伯兰便下到埃及暂住。 11快要到埃及的时候,他对妻子撒莱说:“我知道你是个美貌的女子, 12埃及人看见你,一定会因为你是我的妻子而杀了我,让你活着。 13所以,请你说你是我的妹妹,这样他们会因为你而善待我,留我一命。” 14亚伯兰一行到了埃及撒莱的美貌引起了埃及人的注意。 15法老的官员见了撒莱,就在法老面前称赞她的美貌,她便被带进法老的王宫。 16因为撒莱的缘故,法老厚待亚伯兰,赏给他许多牛、羊、驴、骆驼和仆婢。

17耶和华因亚伯兰妻子撒莱的缘故使法老和他全家患重病。 18法老便召见亚伯兰,说:“你做的是什么事?为什么不告诉我她是你妻子? 19为什么说她是你妹妹,以致我娶她为妻呢?现在你妻子在这里,带她走吧!” 20法老就吩咐人把亚伯兰、他妻子以及他所有的一切都送走了。

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 12:1-20

የአብራም መጠራት

1እግዚአብሔር (ያህዌ) አብራምን እንዲህ አለው፤ “አገርህን፣ ወገንህንና የአባትህን ቤት ትተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ።

2“ታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ፤

ደግሞም እባርክሃለሁ፤

ስምህን ገናና አደርገዋለሁ፤

ለሌሎች በረከት ትሆናለህ።

3የሚባርኩህን እባርካለሁ፤

የሚረግሙህን እረግማለሁ፤

በምድር የሚኖሩ ሕዝቦች፣

በአንተ አማካይነት ይባረካሉ።”

4ስለዚህ አብራም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ወጣ፤ ሎጥም አብሮት ሄደ። አብራም ከካራን ሲወጣ ዕድሜው 75 ዓመት ነበረ። 5አብራምም ሚስቱን ሦራንና የወንድሙን ልጅ ሎጥን አስከትሎ በካራን ሳሉ ያፈሩትን ሀብትና የነበራቸውን አገልጋዮች ይዘው በመጓዝ ከነዓን ምድር ገቡ።

6አብራም ትልቁ የሞሬ ዛፍ እስከሚገኝበት እስከ ሴኬም ድረስ በምድሪቱ ዘልቆ ሄደ። በዚያን ጊዜ ከነዓናውያን በዚሁ ምድር ይኖሩ ነበር። 7እግዚአብሔርም (ያህዌ) ለአብራም ተገልጦ፣ “ይህችን ምድር ለዘርህ እሰጣለሁ” አለው። እርሱም ለተገለጠለት አምላክ (ያህዌ) በዚያ ስፍራ መሠዊያ ሠራ።

8ከዚያም ተነሥቶ ከቤቴል በስተ ምሥራቅ ወዳሉት ተራሮች ሄደ፤ ቤቴልን በምዕራብ፣ ጋይን በምሥራቅ አድርጎ ድንኳን ተከለ፣ በዚያም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሠዊያ ሠራ፤ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ጠርቶ ጸለየ። 9አብራምም ከዚያ ተነሥቶ ወደ ኔጌብ ሄደ።

አብራም በግብፅ አገር

12፥10-20 ተጓ ምብ – ዘፍ 20፥1-1826፥1-11

10በዚያም ምድር ጽኑ ራብ ገብቶ ነበር፤ ከዚህም የተነሣ አብራም ለጥቂት ጊዜ በዚያ ለመኖር ወደ ግብፅ ወረደ። 11ግብፅ ለመግባት ጥቂት ሲቀረው አብራም ሚስቱን ሦራን እንዲህ አላት፤ “መቼም አንቺ ውብ ሴት መሆንሽን ዐውቃለሁ፤ 12ግብፃውያን አንቺን በሚያዩበት ጊዜ፣ ‘ይህች ሚስቱ ናት’ ብለው እኔን ይገድላሉ፤ አንቺን ግን ይተዉሻል። 13ስለዚህ ለአንቺ ሲሉ እንዲንከባከቡኝ፣ ሕይወቴም እንድትተርፍ፣ ‘እኅቱ ነኝ’ በዪ።”

14አብራም በግብፅ አገር እንደ ደረሰ ግብፃውያን፣ ሦራ እጅግ ውብ ሴት እንደ ሆነች አዩ፤ 15የፈርዖንም ሹማምት ባዩአት ጊዜ፣ ለፈርዖን አድንቀው ነገሩት፤ ወደ ቤተ መንግሥትም ወሰዷት። 16በእርሷም ምክንያት ፈርዖን አብራምን አክብሮ አስተናገደው፤ በጎችና ከብቶች፣ ተባዕትና እንስት አህዮች፣ ወንድና ሴት አገልጋዮች እንዲሁም ግመሎችን ሰጠው።

17እግዚአብሔርም (ያህዌ) በአብራም ሚስት በሦራ ምክንያት ፈርዖንንና ቤተ ሰዎቹን በጽኑ ደዌ መታቸው። 18ከዚያም ፈርዖን አብራምን አስጠርቶ እንዲህ አለው፤ “ይህ ያደረግህብን ነገር ምንድን ነው? ‘ሚስትህ እንደ ሆነች ለምን አልነገርኸኝም?’ 19ለምን ‘እኅቴ ናት’ አልኸኝ? ሚስቴ ላደርጋት ነበር። በል አሁንም ሚስትህ ይህችው፤ ይዘሃት ሂድ!” 20ከዚያም ፈርዖን ስለ አብራም ለባለሟሎቹ ትእዛዝ ሰጠ፤ እነርሱም አብራምን ከሚስቱና ከንብረቱ ሁሉ ጋር አሰናበቱት።