出埃及记 31 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

出埃及记 31:1-18

会幕的工匠

1耶和华对摩西说: 2“看啊,在犹大支派中我已经亲自选出户珥的孙子、乌利的儿子比撒列3用我的灵充满他,使他有聪明智慧,精于各种技能和手艺, 4懂得用金、银和铜制造各式各样精巧的器具, 5又能雕刻和镶嵌宝石,精通木工和各种手艺。 6我委派支派亚希撒抹的儿子亚何利亚伯做他的助手。至于其他能工巧匠,我已赐给他们智慧,好照我对你的吩咐制造一切器具, 7即会幕、约柜和约柜上面的施恩座、会幕里面所有的器具、 8桌子和桌上的器具、纯金的灯台和灯台的一切器具、香坛、 9燔祭坛和坛上的一切器具、洗濯盆和盆座, 10还有精工制做的礼服,即亚伦祭司的圣衣及其众子供祭司之职时穿的礼服, 11以及膏油和圣所使用的芬芳的香。他们要照我对你的吩咐去做。”

安息日

12耶和华对摩西说: 13“你要吩咐以色列百姓务必守我的安息日,因为这是我与你们之间世世代代的记号,叫你们知道使你们圣洁的是我耶和华。 14你们要守安息日,以它为圣日。凡不守这诫命的,必被处死。凡在这天工作的,必从民中被铲除。 15一周要工作六天,第七天是庄严的安息日,是耶和华的圣日。凡在安息日做工的,必被处死。 16因此,以色列人世世代代都要守安息日,作为永久的约, 17这是我和以色列人之间永久的记号。耶和华用六天的时间创造天地万物,在第七天停工休息。” 18耶和华在西奈山对摩西说完这些话以后,就把自己用指头刻上诫命的两块石版交给摩西

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 31:1-18

ባስልኤልና ኤልያብ

31፥2-6 ተጓ ምብ – ዘፀ 35፥30-35

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“እነሆ፤ ከይሁዳ ነገድ የሆር የልጅ ልጅ የሆነውን የኡሪን ልጅ ባስልኤልን መርጬዋለሁ። 3በሁሉም ዐይነት የእጅ ጥበብ ሥራ፣ ብልኀት፣ ችሎታና ዕውቀት እንዲኖረው የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም) መንፈስ ሞልቼዋለሁ። 4ይኸውም በወርቅ፣ በብርና በናስ ለሚሠሩት ሥራዎች በጥበብ የተሠሩ ጌጦችን እንዲያበጅ፣ 5ድንጋዮችን እንዲቈፍርና እንዲጠርብ ከዕንጨትም ጥርብ እንዲያወጣ፣ ሁሉንም ዐይነት የእጅ ጥበብ ሥራዎችን እንዲያከናውን ነው። 6በተጨማሪም ከዳን ነገድ የሆነውን የአሂሳሚክን ልጅ ኤልያብን እንዲረዳው መርጬዋለሁ፤ እንዲሁም ያዘዝሁህን ሁሉ ያደርጉ ዘንድ ለእጅ ጥበብ ዐዋቂዎች ሁሉ ብልኀትን ሰጥቻቸዋለሁ፤

7“ይኸውም የመገናኛውን ድንኳን፣

የምስክሩን ታቦት በላዩ ላይ ካለው ከስርየት መክደኛው ጋር፣

ሌሎች የድንኳኑን መገልገያ ዕቃዎች ሁሉ፣

8ጠረጴዛውን ከነዕቃዎቹ፣

ከንጹሕ ወርቅ የተሠራውን የወርቅ መቅረዝ ከነዕቃዎቹ፣

የዕጣኑን መሠዊያ፣

9የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውን ከነዕቃዎቹ፣

ሰኑን፣ ከነማስቀመጫው፣

10ከፈትል የተሠሩ ልብሶችን ይኸውም የካህኑን የአሮንን የተቀደሱ ልብሶችንና ካህናት ሆነው ሲያገለግሉ የሚለብሷቸውን የወንድ ልጆቹ ልብሶች፣

11እንዲሁም የመቅደሱ የሆነውን ቅብዐ ዘይትና ጣፋጭ ሽታ ያለውን ዕጣን እንዲሠሩ ነው።

“ልክ እኔ እንዳዘዝሁህ ያብጇቸው።”

ሰንበት

12ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 13“ለእስራኤላውያን ንገራቸው፤ ‘ሰንበቴን ማክበር አለባችሁ፤ ይህም በእኔና በእናንተ መካከል በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ምልክት ይሆናል፤ ይኸውም የምቀድሳችሁ31፥13 ወይም፣ ቅዱስ አድርጌ የምለያችሁ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ሆንሁ እንድታውቁ ነው።

14“ ‘ለእናንተ ቅዱስ ነውና ሰንበትን አክብሩ፤ ማንም ቢሽረው በሞት ይቀጣል፤ በዚያ ቀን ማንም የሚሠራ ቢኖር ከወገኑ ተነጥሎ ይለይ። 15ስድስት ቀን ሥራ ይሠራል፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ የዕረፍት ሰንበት ነው፤ በሰንበት ቀን ማንም ቢሠራ በሞት መቀጣት አለበት። 16እስራኤላውያን በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ሰንበትን በመጠበቅ የዘላለም ኪዳን አድርገው ማክበር አለባቸው፤ 17በእኔና በእስራኤላውያን መካከል ለዘላለም ምልክት ይሆናል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሰማይንና ምድርን በስድስት ቀን ሠርቶ፣ በሰባተኛው ቀን ከሥራ ታቅቦ ዐርፏልና።’ ”

18እግዚአብሔር (ያህዌ) በሲና ተራራ ላይ ለሙሴ መናገሩን ከፈጸመ በኋላ፣ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም) ጣት የተጻፈባቸውን የድንጋይ ጽላቶች፣ ሁለቱን የምስክር ጽላቶች ለእርሱ ሰጠው።