亚古珥的箴言
1以下是雅基的儿子亚古珥的箴言。
这人说:上帝啊,我很疲倦;
上帝啊,我很疲倦,精疲力尽。30:1 希伯来文或译“这人对以铁说,对以铁和乌甲说:”
2我比众人都愚蠢,
不具备人的悟性。
3我从未学到智慧,
也不认识至圣者。
4谁升上高天又降下来?
谁将风聚在掌中?
谁将众水裹在衣服里?
谁定了地的边界?
祂叫什么名字?
祂儿子叫什么名字?
你知道吗?
5上帝的话句句千真万确,
祂作投靠祂之人的盾牌。
6你不可对祂的话有所添加,
免得祂责备你,
揭穿你的虚谎。
7上帝啊,我向你求两件事,
求你在我未死以前赐给我。
8求你使虚伪和谎言远离我,
求你让我不贫穷也不富足,
赐给我需用的饮食,
9免得我因为饱足就不认你,
说:“耶和华是谁呢?”
又恐怕我因穷困而偷窃,
以致辱没我上帝的名。
10别向主人毁谤他的仆人,
免得你受咒诅、担当罪责。
11有一种30:11 “种”希伯来文是“世代”,11-14节也相同。人咒诅父亲,
不为母亲祝福。
12有一种人自以为纯洁,
却没有洗掉自己的污秽。
13有一种人趾高气扬,
目空一切。
14有一种人牙如剑,
齿如刀,
要吞吃世间的困苦人和贫穷人。
15水蛭有两个女儿,
她们不停地叫:“给我!给我!”
三样东西从不知足,
永不言“够”的共有四样:
16阴间、不孕的妇人、
干旱的土地和火焰。
17嘲笑父亲、藐视母亲教诲的,
眼睛必被谷中的乌鸦啄出,
被秃鹰吃掉。
18我测不透的妙事有三样,
我不明白的事共有四样:
19鹰在空中飞翔之道,
蛇在石上爬行之道,
船在海中航行之道,
男女相爱之道。
20淫妇的道是这样:
她吃完就擦擦嘴,
说,“我没有做坏事。”
21使大地震动的事有三样,
大地无法承受的事共有四样:
22奴仆做王,
愚人吃饱,
23丑恶女子出嫁,
婢女取代主母。
24地上有四种动物,
身体虽小却极其聪明:
25蚂蚁力量虽小,
却在夏天储备粮食;
26石獾虽不强壮,
却在岩石中筑巢穴;
27蝗虫虽无君王,
却整齐地列队前进;
28壁虎虽易捕捉,
却居住在王宫大内。
29步履威武的有三样,
走路雄壮的共有四样:
30威震百兽、从不畏缩的狮子,
31昂首阔步的雄鸡,
公山羊和率领军队的君王。
32你若行事愚昧、
妄自尊大或图谋不轨,
就当用手掩口。
33激起愤怒会引起争端,
正如搅牛奶会搅出奶油,
拧鼻子会拧出血。
አጉር የተናገራቸው ምሳሌዎች
1የያቄ ልጅ የአጉር ቃል ይህ ነው፤30፥1 ወይም የማሳው ያቄ
ይህ ሰው ለኢቲኤል፣
ለኢቲኤልና ለኡካል ተናገረ፤30፥1 የማስሬቲክ ጽሑፍ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የዕብራይስጡ ግን ተናገረ፤ አቤቱ እግዚአብሔር፤ እኔ ደክሜአለሁ፣ ነገር ግን እጸናለሁ ይላል።
2“እኔ ከሰው ሁሉ ይልቅ ጅል ነኝ፤
ሰው ያለው ማስተዋል የለኝም።
3ጥበብን አልተማርሁም፤
ስለ ቅዱሱም ዕውቀት የለኝም።
4ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው?
ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው?
ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው?
የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው?
ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል?
የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!
5“የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንከን የለበትም፤
እርሱ ለሚታመኑበት ሁሉ ጋሻቸው ነው።
6በእርሱ ቃል ላይ አንዳች አትጨምር፤
አለዚያ ይዘልፍሃል፤ ሐሰተኛም ያደርግሃል።
7“እግዚአብሔር ሆይ፤ ሁለት ነገር እለምንሃለሁ፤
እነዚህንም ከመሞቴ በፊት አትከልክለኝ፤
8ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤
ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤
ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።
9አለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤
‘እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤
ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤
የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።
10“አገልጋይን በጌታው ፊት በክፉ አታንሣው፤
አለዚያ ይረግምህና ጕዳት ያገኝሃል።
11“አባቱን የሚረግም፣
እናቱን የማይባርክ ትውልድ አለ፤
12ራሳቸውን ንጹሓን አድርገው የሚቈጥሩ፣
ሆኖም ከርኩሰታቸው ያልነጹ አሉ፤
13ዐይናቸው ትዕቢተኛ የሆነ፣ አስተያያቸው ንቀት የሞላበት፣
14ድኾችን ከምድር፣
ችግረኞችንም ከሰው ዘር መካከል ለማጥፋት፣
ጥርሳቸው ሰይፍ የሆነ፣
መንጋጋቸውም ካራ የሆነ አሉ።
15“አልቅት ሁለት ሴት ልጆች አሉት፤
‘ስጡን! ስጡን!’ እያሉ ይጮኻሉ፤
“ፈጽሞ የማይጠግቡ ሦስት ነገሮች አሉ፤
‘በቃኝን’ ከቶ የማያውቁ አራት ናቸው፤
16እነርሱም መቃብር፣30፥16 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። መካን ማሕፀን፣
ውሃ ጠጥታ የማትረካ ምድር፣
‘በቃኝ’ የማይል እሳት ናቸው።
17“በአባት ላይ የምታፌዝ ዐይን፣
የእናትንም ትእዛዝ የምትንቅ፣
የሸለቆ ቍራዎች ይጐጠጕጧታል፤
ጆፌ አሞሮችም ይበሏታል።
18“እጅግ የሚያስደንቁኝ ሦስት ነገሮች አሉ፤
የማላስተውላቸውም አራት ናቸው፤
19የንስር መንገድ በሰማይ፣
የእባብ መንገድ በቋጥኝ፣
የመርከብ መንገድ በባሕር፣
የሰውም መንገድ ከሴት ልጅ ጋር ናቸው።
20“የአመንዝራዪቱ መንገድ ይህ ነው፤
በልታ አፏን በማበስ፣
‘ምንም የሠራሁት ጥፋት የለም’ ትላለች።
21“ምድር በሦስት ነገር ትናወጣለች፤
እንዲያውም መሸከም የማትችላቸው አራት ነገሮች ናቸው፤
22ባሪያ ሲነግሥ፣
ሰነፍ እንጀራ ሲጠግብ፣
23የተጠላች ሴት ባል ስታገባ፣
ሴት ባሪያ በእመቤቷ እግር ስትተካ።
24“በምድር ላይ አራት ነገሮች ትንንሽ ናቸው፤
ሆኖም እጅግ ጠቢባን ናቸው፤
25ጕንዳኖች ደካማ ፍጡራን ናቸው፤
ሆኖም ምግባቸውን በበጋ ያከማቻሉ።
26ሽኮኮዎች ዐቅመ ደካማ ናቸው፤
ሆኖም መኖሪያቸውን በቋጥኞች መካከል ይሠራሉ፤
27አንበጦች ንጉሥ የላቸውም፤
ሆኖም ቅደም ተከተል ይዘው ይጓዛሉ፤
28እንሽላሊት በእጅ ትያዛለች፤
ሆኖም በቤተ መንግሥት ትገኛለች።
29“አረማመዳቸው ግርማዊ የሆነ ሦስት ነገሮች አሉ፤
እንዲያውም በሞገስ የሚጐማለሉ አራት ናቸው፤
30ከአራዊት መካከል ኀይለኛ የሆነው፣
ከምንም ነገር ፊት ግንባሩን የማያጥፈው አንበሳ፤
31ጐርደድ ጐርደድ የሚል አውራ ዶሮ፣ አውራ ፍየል፣
እንዲሁም በሰራዊቱ የታጀበ ንጉሥ ናቸው።30፥31 ወይም ከተቃውሞ የተጠበቀ ንጉሥ
32“ተላላ ሆነህ ራስህን ከፍ ከፍ ካደረግህ፣
ወይም ክፉ ነገር ካቀድህ፣
እጅህን በአፍህ ላይ አድርግ።
33ወተት ሲናጥ ቅቤ እንደሚወጣው፣
አፍንጫን ሲያሹት እንደሚደማ፣
ቍጣን ማነሣሣትም ጥልን ይፈጥራል።”