1温和的回答平息怒气,
粗暴的言词激起愤怒。
2智者的舌头传扬知识,
愚人的嘴巴吐露愚昧。
3耶和华的眼目无所不在,
善人和恶人都被祂鉴察。
4温和的言词带来生命,
乖谬的话语伤透人心。
5愚人蔑视父亲的管教,
接受责备的才算明智。
6义人家中财富充足,
恶人得利惹来祸患。
7智者的嘴传扬知识,
愚人的心并非如此。
8耶和华憎恨恶人的祭物,
悦纳正直人的祈祷。
9耶和华憎恨恶人的行径,
喜爱追求公义的人。
10背离正道,必遭严惩;
厌恶责备,必致死亡。
11阴间和冥府15:11 “冥府”希伯来文是“亚巴顿”,参考启示录9:11。在耶和华面前尚且无法隐藏,
何况世人的心思呢!
12嘲讽者不爱听责备,
也不愿请教智者。
13心中喜乐,容光焕发;
心里悲伤,精神颓丧。
14哲士渴慕知识,
愚人安于愚昧。
15困苦人天天受煎熬,
乐观者常常有喜乐。
16财物虽少但敬畏耶和华,
胜过家财万贯却充满烦恼。
17粗茶淡饭但彼此相爱,
胜过美酒佳肴却互相憎恨。
18脾气暴躁,惹起争端;
忍耐克制,平息纠纷。
19懒惰人的路布满荆棘,
正直人的道平坦宽阔。
20智慧之子使父亲欢喜,
愚昧的人却藐视母亲。
21无知者以愚昧为乐,
明哲人遵循正道。
22独断专行,计划失败;
集思广益,事无不成。
23应对得体,心中愉快;
言语合宜,何等美好!
24智者循生命之路上升,
以免坠入阴间。
25耶和华拆毁傲慢人的房屋,
祂使寡妇的地界完整无损。
26耶和华憎恨恶人的意念,
喜爱纯洁的言语。
27贪爱财富,自害己家;
厌恶贿赂,安然存活。
28义人三思而后答,
恶人张口吐恶言。
29耶和华远离恶人,
却听义人的祷告。
30笑颜令人心喜,
喜讯滋润骨头。
31倾听生命的训诫,
使人与智者同列。
32不受管教就是轻看自己,
听从责备才能得到智慧。
33敬畏耶和华使人得智慧,
学会谦卑后才能得尊荣。
1የለዘበ መልስ ቍጣን ያበርዳል፤
ክፉ ቃል ግን ቍጣን ይጭራል።
2የጠቢብ አንደበት ዕውቀትን ታወድሳለች፤
የተላሎች አንደበት ግን ቂልነትን ያፈልቃል።
3የእግዚአብሔር ዐይኖች በሁሉም ስፍራ ናቸው፤
ክፉዎችንም ደጎችንም ነቅተው ይመለከታሉ።
4ፈውስ የምታመጣ ምላስ የሕይወት ዛፍ ናት፤
አታላይ ምላስ ግን መንፈስን ትሰብራለች።
5ተላላ የአባቱን ምክር ይንቃል፤
መታረምን የሚቀበል ግን አስተዋይነቱን ያሳያል።
6የጻድቃን ቤት በብዙ ሀብት የተሞላ ነው፤
የክፉዎች ገቢ ግን መከራን ታመጣባቸዋለች።
7የጠቢባን ከንፈር ዕውቀትን ታስፋፋለች፤
የተላሎች ልብ ግን እንዲህ አይደለም።
8እግዚአብሔር የክፉዎችን መሥዋዕት ይጸየፋል፤
የቅኖች ጸሎት ግን ደስ ያሰኘዋል።
9እግዚአብሔር የክፉዎችን መንገድ ይጸየፋል፤
ጽድቅን የሚከታተሉትን ግን ይወድዳቸዋል።
10ከመንገድ የሚወጣ ሰው ጥብቅ ቅጣት ይጠብቀዋል፤
ዕርምትን የሚጠላ ይሞታል።
11ሲኦልና የሙታን ዓለም15፥11 በዕብራይስጡ ሲኦልና አባዶን ይላል። በእግዚአብሔር ፊት የተገለጡ ናቸው፤
የሰዎች ልብማ የቱን ያህል የታወቀ ነው!
12ፌዘኛ መታረምን ይጠላል፤
ጠቢባንንም አያማክርም።
13ደስተኛ ልብ ፊትን ያፈካል፤
የልብ ሐዘን ግን መንፈስን ይሰብራል።
14አስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይሻል፤
የተላላ አፍ ግን ቂልነትን ያመነዥካል።
15የተጨቈኑ ሰዎች ዘመናቸው ሁሉ የከፋ ነው፤
በደስታ የተሞላ ልብ ግን የማይቋረጥ ፈንጠዝያ አለው።
16እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር፣
ሁከት ካለበት ትልቅ ሀብት ይበልጣል።
17ፍቅር ባለበት ጐመን መብላት፣
ጥላቻ ባለበት የሰባ ፍሪዳ ከመብላት ይሻላል።
18ግልፍተኛ ሰው ጠብ ያነሣሣል፤
ታጋሽ ሰው ግን ጠብን ያበርዳል።
19የሀኬተኛ መንገድ በእሾኽ የታጠረች ናት፤
የቅኖች መንገድ ግን የተጠረገ አውራ ጐዳና ነው።
20ጠቢብ ልጅ አባቱን ደስ ያሰኛል፤
ተላላ ሰው ግን እናቱን ይንቃል።
21ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤
አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።
22ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤
በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።
23ሰው ተገቢ መልስ በመስጠት ደስታን ያገኛል፤
በወቅቱም የተሰጠ ቃል ምንኛ መልካም ነው!
24ወደ ሲኦል15፥24 ወይም መቃብር ከመውረድ እንዲድን፣
የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።
25እግዚአብሔር የትዕቢተኛውን ቤት ያፈርሰዋል፤
የመበለቲቱን ዳር ድንበር ግን እንዳይደፈር ይጠብቃል።
26እግዚአብሔር የክፉውን ሰው ሐሳብ ይጸየፋል፤
የንጹሓን ሐሳብ ግን ደስ ያሰኘዋል።
27ስስታም ሰው በቤተ ሰቡ ላይ ችግር ያመጣል፤
ጕቦን የሚጠላ ግን በሕይወት ይኖራል።
28የጻድቅ ሰው ልብ የሚሰጠውን መልስ ያመዛዝናል፤
የክፉ ሰው አፍ ግን ክፋትን ያጐርፋል።
29እግዚአብሔር ከክፉዎች ሩቅ ነው፤
የጻድቃንን ጸሎት ግን ይሰማል።
30ብሩህ ገጽታ ልብን ደስ ያሰኛል፤
መልካም ዜናም ዐጥንትን ያለመልማል።
31ሕይወት ሰጭ የሆነውን ተግሣጽ የሚሰማ፣
በጠቢባን መካከል ይኖራል።
32ተግሣጽን የሚንቅ ራሱን ይንቃል፤
ዕርምትን የሚቀበል ግን ማስተዋልን ያገኛል።
33እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብን መማር ነው፤15፥33 ወይም ጥበብ እግዚአብሔርን መፍራት ታስተምራለች።
ትሕትናም ክብርን ትቀድማለች።