โยบ 8 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

โยบ 8:1-22

บิลดัด

1บิลดัดชาวชูอาห์โต้ตอบโยบว่า

2“ท่านจะพูดเช่นนี้ไปอีกนานเท่าใด

ถ้อยคำของท่านเป็นดั่งพายุบุแคม

3พระเจ้าทรงบิดเบือนความยุติธรรมหรือ?

องค์ทรงฤทธิ์บิดเบือนความถูกต้องหรือ?

4หากบุตรหลานของท่านทำบาปต่อพระองค์

พระองค์ก็ทรงลงโทษพวกเขา

5แต่ถ้าท่านหมายพึ่งพระเจ้า

ทูลวิงวอนองค์ทรงฤทธิ์

6หากท่านบริสุทธิ์และชอบธรรม

พระองค์จะทรงลุกขึ้นเพื่อท่าน

แล้วนำท่านคืนสู่ฐานะอันสมควรแก่ท่าน

7ถึงแม้ว่าท่านจะเริ่มต้นด้วยสิ่งเล็กน้อย

อนาคตของท่านก็ยังจะเจริญรุ่งเรือง

8“จงถามคนรุ่นก่อนดู

แล้วท่านจะค้นพบสิ่งที่บรรพบุรุษได้เรียนรู้

9เพราะเราเพิ่งเกิดมาเมื่อวานนี้เท่านั้น และไม่รู้อะไร

และวันเวลาของเราในโลกนี้ก็เป็นเพียงเงา

10บรรพบุรุษจะไม่บอกกล่าวเล่าสอนหรือ?

จะไม่พูดให้ท่านฟังจากความเข้าใจของพวกเขาหรอกหรือ?

11ต้นกกจะขึ้นงามในที่ซึ่งไม่มีห้วยหนองคลองบึงหรือ?

ต้นอ้อจะอยู่ได้โดยปราศจากน้ำหรือ?

12และทั้งๆ ที่พวกมันยังงอกงาม ไม่มีใครมาตัด

มันก็ยังเหี่ยวเฉาไปเร็วกว่าต้นหญ้าฉันใด

13บั้นปลายของผู้ที่หลงลืมพระเจ้าก็เป็นไปฉันนั้น

ความหวังของผู้ที่ไม่มีพระเจ้าก็พินาศไป

14สิ่งที่เขาพึ่งพาก็เปราะบาง8:14 ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจน

สิ่งที่เขาพึ่งพิงเป็นแค่ใยแมงมุม

15เขาหวังพักพิง แต่มันก็ขาดไป

เขายึดกุมไว้ แต่มันก็ไม่คงอยู่

16เขาเหมือนต้นไม้ที่ได้รับน้ำชุ่มชื่นกลางแดด

แผ่แขนงไปในสวน

17รากของเขาหยั่งลงไปในกองหิน

เสาะหาที่จะชอนไชไป

18แต่เมื่อถูกหักโค่นไป

ถิ่นนั้นก็ตัดขาดจากมันและกล่าวว่า ‘เราไม่เคยเห็นเจ้ามาก่อน’

19แน่ทีเดียว ชีวิตของมันก็เหี่ยวเฉาไป

และ8:19 หรือแน่ทีเดียว ความชื่นชมยินดีทั้งหมดที่มี / ก็คือมีพืชอื่นๆ งอกขึ้นมาแทนที่

20“แน่ทีเดียว พระเจ้าย่อมไม่ทอดทิ้งคนที่ดีพร้อม

ทั้งจะไม่ค้ำจุนคนทำชั่ว

21พระองค์จะยังคงให้ปากของท่านหัวเราะร่า

และให้ริมฝีปากของท่านโห่ร้องยินดี

22ศัตรูของท่านจะเต็มไปด้วยความอับอาย

เต็นท์ของคนชั่วร้ายจะไม่มีอีกต่อไป”

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 8:1-22

በልዳዶስ

1ሹሐዊውም በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“እንዲህ ያለውን ነገር የምትናገረው፣

ቃልህም እንደ ብርቱ ነፋስ የሚሆነው እስከ መቼ ነው?

3እግዚአብሔር ፍትሕን ያጣምማልን?

ሁሉን ቻይ አምላክስ ጽድቅን ያጣምማልን?

4ልጆችህ በእርሱ ላይ ኀጢአት ሠርተው ከሆነ፣

ለኀጢአታቸው ቅጣት አሳልፎ ሰጥቷቸዋል።

5ነገር ግን አንተ ወደ እግዚአብሔር ብትመለከት፣

ሁሉን ቻይ አምላክን ብትማፀን፣

6ንጹሕና ቅን ብትሆን፣ እርሱ ስለ አንተ አሁኑኑ ይነሣል፤

ወደ ተገቢውም ስፍራህ ይመልስሃል።

7ጅማሬህ አነስተኛ ቢመስልም፣

ፍጻሜህ እጅግ ታላቅ ይሆናል።

8“የቀደመውን ትውልድ ጠይቅ፤

አባቶቻቸውም የደረሱበትን መርምረህ አግኝ፤

9እኛ ትናንት ስለ ተወለድን አንዳች አናውቅምና፤

ዘመናችንም በምድር ላይ እንደ ጥላ ነው።

10እነርሱ የሚያስተምሩህና የሚነግሩህ፣

ከልቦናቸውም ቃልን የሚያወጡ አይደሉምን?

11ደንገል ረግረግ በሌለበት ስፍራ ይበቅላልን?

ቄጠማስ ውሃ በሌለበት ይለመልማልን?

12ገና በማደግ ላይ እያለ ሳይታጨድ፣

ከሌሎች ዕፀዋት ፈጥኖ ይደርቃል።

13እግዚአብሔርን የሚረሱ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤

አምላክ የለሽ ኑሮ የሚኖሩም ሁሉ ተስፋቸው ትጠፋለች።

14መተማመኛው ቀጭን ክር፣8፥14 በዕብራይስጥ የዚህ ቃል ትርጕም አይታወቅም።

ድጋፉም የሸረሪት ድር ነው።

15ድሩ ላይ ቢደገፍ ይበጠስበታል፤

አጥብቆም ቢይዘው አይጸናም።

16ውሃ እንደ ጠገበ ተክል፣ ፀሓይ እየሞቀው፣

ቅርንጫፉን ሁሉ በአትክልቱ ስፍራ ላይ ይዘረጋል።

17ሥሩን በድንጋይ ክምር ላይ ይጠመጥማል፤

በዐለትም መካከል ስፍራ ያበጃል።

18ከስፍራው ሲወገድ ግን፣

ያ ቦታ ‘አይቼህ አላውቅም’ ብሎ ይክደዋል።

19እነሆ፤ ሕይወቱ በዚህ ያከትማል፤8፥19 ወይም ያለው ደስታ ሁሉ

ሌሎች አትክልትም ከመሬት ይበቅላሉ።

20“እነሆ፤ እግዚአብሔር እንከን የሌለበትን ሰው አይጥልም፤

የክፉዎችንም እጅ አያበረታም፤

21እንደ ገና አፍህን በሣቅ፤

ከንፈሮችህንም በእልልታ ይሞላል።

22ጠላቶችህ ኀፍረት ይለብሳሉ፤

የክፉዎችም ድንኳን ይጠፋል።”