สุภาษิต 9 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

สุภาษิต 9:1-18

คำเชื้อเชิญของปัญญาและความโง่เขลา

1ปัญญาได้สร้างบ้านขึ้นบนเสาหลักเจ็ดต้น

2นางได้เตรียมเนื้อและผสมเหล้าองุ่นไว้

แล้วได้จัดโต๊ะอาหารของนางไว้ด้วย

3แล้วส่งสาวใช้ออกไปเชื้อเชิญทุกคน

ปัญญาร้องเรียกจากจุดสูงสุดของเมืองว่า

4“ให้บรรดาคนอ่อนต่อโลกมาที่บ้านของเราเถิด!”

นางกล่าวกับคนไร้สามัญสำนึกว่า

5“เชิญมารับประทานอาหาร

และดื่มเหล้าองุ่นที่เราได้ผสมไว้

6จงทิ้งวิถีอันอ่อนต่อโลกของเจ้า แล้วเจ้าจะมีชีวิตอยู่

จงดำเนินในวิถีแห่งความเข้าใจ”

7“ผู้ที่ตักเตือนคนชอบเยาะเย้ย มีแต่จะถูกตอกกลับ

ผู้ที่ตักเตือนคนชั่วร้าย มีแต่จะถูกทำร้าย

8อย่าไปว่ากล่าวคนชอบเยาะเย้ย ไม่อย่างนั้นเขาจะเกลียดชังเจ้า

จงตักเตือนคนฉลาด แล้วเขาจะรักเจ้า

9จงสอนคนฉลาด แล้วเขาจะฉลาดยิ่งขึ้น

จงสอนคนชอบธรรม แล้วเขาจะเรียนรู้มากขึ้น

10“ความยำเกรงองค์พระผู้เป็นเจ้าเป็นที่เริ่มต้นของปัญญา

การรู้จักองค์บริสุทธิ์ทำให้เกิดความเข้าใจ

11เพราะเรา วันเวลาของเจ้าจะยืนยาว

และปีเดือนแห่งชีวิตของเจ้าจะเพิ่มพูน

12หากเจ้าฉลาด สติปัญญาของเจ้าจะให้บำเหน็จแก่เจ้า

หากเจ้าชอบเยาะเย้ย เจ้าก็จะทนทุกข์ตามลำพัง”

13ผู้หญิงที่ได้ชื่อว่า “โง่” ชอบพูดพล่าม

นางไร้ระเบียบวินัยและไม่รู้อะไรเลย

14นางนั่งอยู่ที่ประตูบ้าน

หรือในที่สูงของเมือง

15คอยร้องเรียกผู้คนที่ผ่านไปผ่านมา

ผู้มุ่งหน้าไปตามทางของตน

16“ให้บรรดาคนอ่อนต่อโลก มาที่บ้านของเราเถิด!”

นางกล่าวกับบรรดาคนไร้สามัญสำนึกว่า

17“น้ำที่ลักเขาดื่มก็ชื่นใจดี

อาหารที่แอบเขากินก็เอร็ดอร่อย!”

18แต่คนเหล่านั้นหารู้ไม่ว่าที่นั่นมีแต่คนตาย

และแขกของนางล้วนอยู่ก้นหลุมฝังศพ

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 9:1-18

ጠቢብነትና ተላላነት

1ጥበብ ቤቷን ሠራች፤

ሰባቱን ምሰሶዎቿንም ጠርባ አቆመች፤

2ፍሪዳዋን ዐረደች፤ የወይን ጠጇን ጠመቀች፤

ማእዷንም አዘጋጀች።

3ሴት አገልጋዮቿንም ላከች፤

ከከተማዪቱም ከፍተኛ ቦታ ተጣራች።

4እርሷም ማመዛዘን ለጐደላቸው፣

“ማስተዋል የሌላችሁ ሁሉ ወደዚህ ኑ” አለች።

5“ኑ፤ ምግቤን ተመገቡ፤

የጠመቅሁትንም የወይን ጠጅ ጠጡ።

6የሞኝነት መንገዳችሁን ተዉ፤ በሕይወት ትኖራላችሁ፤

በማስተዋልም መንገድ ተመላለሱ።”

7ፌዘኛን የሚገሥጽ ሁሉ ስድብን በራሱ ላይ ያመጣል፤

ክፉውን ሰው የሚዘልፍ ሁሉ ውርደት ያገኘዋል።

8ፌዘኛን አትዝለፈው፤ ይጠላሃል፤

ጠቢብን ገሥጸው፤ ይወድድሃል።

9ጠቢብን አስተምረው፣ ይበልጥ ጥበበኛ ይሆናል፤

ጻድቁን ሰው አስተምረው፤ ዕውቀቱን ይጨምራል።

10“የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤

ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል ነው።

11ዘመንህ በእኔ ምክንያት ይረዝማልና፤

ዕድሜም በሕይወትህ ላይ ይጨመርልሃል።

12ጠቢብ ብትሆን ጥበበኛነትህ ለራስህ ነው፤

ፌዘኛ ብትሆን የምትጐዳው ያው አንተው ነህ።”

13ጥበብ የለሽ ሴት ለፍላፊ ናት፤

እርሷም ስድና ዕውቀት የለሽ ናት።

14በቤቷ ደጃፍ ላይ ትጐለታለች፤

በከተማዪቱ ከፍተኛ ቦታ በመቀመጫ ላይ ትቀመጣለች።

15በዚያ የሚያልፉትን፣

መንገዳቸውን ይዘው የሚሄዱትን ትጣራለች።

16እርሷም ማመዛዘን ለጐደላቸው፣

“ማስተዋል የሌላችሁ ሁሉ ወደዚህ ኑ” ትላለች።

17“የስርቆት ውሃ ይጣፍጣል፤

ተሸሽገው የበሉት ምግብ ይጥማል።”

18እነርሱ ግን ሙታን በዚያ እንዳሉ፣

ተጋባዦቿም በሲኦል9፥18 ወይም መቃብር ጥልቀት ውስጥ እንደ ሆኑ አያውቁም።