สดุดี 64 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 64:1-10

สดุดี 64

(ถึงหัวหน้านักร้อง บทสดุดีของดาวิด)

1ข้าแต่พระเจ้า ขอทรงฟังคำร้องทุกข์ของข้าพระองค์

ขอทรงปกป้องชีวิตข้าพระองค์ให้พ้นจากการคุกคามของเหล่าศัตรู

2ขอทรงซ่อนข้าพระองค์ให้พ้นจากการสมรู้ร่วมคิดของเหล่าคนชั่ว

ให้พ้นจากอุบายของพวกคนชั่ว

3พวกเขาลับลิ้นของตนอย่างลับดาบ

และพ่นวาจาดั่งยิงธนูอาบยาพิษ

4พวกเขายิงใส่ผู้บริสุทธิ์จากที่ซุ่ม

พวกเขายิงทันทีอย่างไม่เกรงกลัว

5เขาปลุกใจซึ่งกันและกันในการวางแผนชั่ว

พวกเขาพูดกันเรื่องวางกับดักล่อเหยื่อ

เขาพูดว่า “ใครจะเห็นมัน64:5 หรือพวกเรา?”

6พวกเขาวางแผนการที่อยุติธรรมและพูดว่า

“เราได้วางแผนไว้อย่างยอดเยี่ยม!”

แน่นอน ความคิดและจิตใจของมนุษย์นั้นเจ้าเล่ห์นัก

7แต่พระเจ้าเองจะทรงยิงธนูใส่เขา

เขาจะถูกโค่นล้มโดยไม่ทันรู้ตัว

8พระองค์จะทำให้พวกเขาย่อยยับด้วยลิ้นของตนเอง

ทุกคนที่เห็นเขาจะส่ายหน้าเย้ยหยัน

9มวลมนุษยชาติจะเกรงกลัว

จะป่าวประกาศพระราชกิจของพระเจ้า

และใคร่ครวญสิ่งที่พระองค์ได้ทรงกระทำ

10ให้คนชอบธรรมชื่นชมยินดีในองค์พระผู้เป็นเจ้า

และลี้ภัยในพระองค์

ให้ผู้มีจิตใจเที่ยงธรรมสรรเสริญพระองค์เถิด!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 64:1-10

መዝሙር 64

የተሳዳቢዎች ቅጣት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1አምላክ ሆይ፤ የብሶት ቃሌን ስማ፤

ሕይወቴንም ከሚያስፈራ የጠላት ዛቻ ከልላት።

2ከክፉዎች አድማ ሰውረኝ፤

ከዐመፀኞችም ሸንጎ ጋርደኝ።

3እነርሱ ምላሳቸውን እንደ ሰይፍ ይስላሉ፤

መርዘኛ ቃላቸውንም እንደ ፍላጻ ያነጣጥራሉ።

4አሸምቀው ንጹሑን ሰው ይነድፉታል፤

ድንገት ይነድፉታል፤ አይፈሩምም።

5ክፉ ተግባር ለማከናወን እርስ በርስ ይመካከራሉ፤

በስውር ወጥመድ ለመዘርጋት ይነጋገራሉ፤

“ማንስ ሊያየን ይችላል?”64፥5 ወይም ማንስ ሊያያቸው ይችላል ይባባላሉ።

6ግፍን ያውጠነጥናሉ፤

ደግሞም፣ “የረቀቀች ሤራ አዘጋጅተናል” ይላሉ፤

አቤት! የሰው ልቡ፣ አእምሮውም እንዴት ጥልቅ ነው!

7እግዚአብሔር ግን በፍላጻው ይነድፋቸዋል፤

እነርሱም ድንገት ይቈስላሉ።

8በገዛ ምላሳቸው ያሰናክላቸዋል፤

ጥፋትንም ያመጣባቸዋል፤

የሚያዩአቸውም ሁሉ በትዝብት ራሳቸውን ይነቀንቃሉ።

9የሰው ልጆች ሁሉ ይፈራሉ፤

የእግዚአብሔርን ሥራ በይፋ ያወራሉ፤

ያደረገውንም በጥሞና ያሰላስላሉ።

10ጻድቅ በእግዚአብሔር ደስ ይበለው፤

እርሱንም መጠጊያ ያድርገው፤

ልበ ቅኖችም ሁሉ ደስ ይበላቸው።