สดุดี 48 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

สดุดี 48:1-14

สดุดี 48

(เพลงบทหนึ่ง บทสดุดีของบุตรโคราห์)

1องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงยิ่งใหญ่ และควรแก่การสรรเสริญเป็นที่สุด

ในนครแห่งพระเจ้าของเราภูเขาอันศักดิ์สิทธิ์ของพระองค์

2ศิโยนนั้นสูงเด่นงามตายิ่งนัก

เป็นความปีติยินดีของคนทั่วโลก

ดั่งยอดสูงสุดของซาโฟน48:2 อาจหมายถึง ภูเขาศักดิ์สิทธิ์ หรือ ทางด้านทิศเหนือ

ศิโยนนคร48:2 หรือคนทั่วโลก / ภูเขาศิโยนทางด้านเหนือ / ของนครแห่งองค์จอมราชัน

3พระเจ้าทรงประทับในป้อมของนครนั้น

พระองค์ทรงสำแดงพระองค์เองเป็นปราการของนคร

4เมื่อบรรดากษัตริย์รวมกำลังกัน

เมื่อพวกเขารุดหน้าไปด้วยกัน

5พวกเขาอัศจรรย์ใจเมื่อเห็นนครนั้น

พวกเขาพากันหนีไปด้วยความกลัว

6พวกเขาหวาดหวั่นขวัญผวา

เจ็บปวดดั่งผู้หญิงที่กำลังคลอดบุตร

7พระองค์ทรงทำลายพวกเขาให้เป็นเหมือนเรือแห่งทารชิช

ซึ่งแตกเป็นเสี่ยงๆ ด้วยลมตะวันออก

8เราได้ยินมาอย่างไร

เราก็ได้เห็นอย่างนั้นว่า

ในนครของพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์

ในนครของพระเจ้าของเรา

พระเจ้าทรงทำให้นครนั้นมั่นคง

นิรันดร์

เสลาห์

9ข้าแต่พระเจ้า ภายในพระวิหารของพระองค์

ข้าพระองค์ทั้งหลายใคร่ครวญถึงความรักมั่นคงของพระองค์

10ข้าแต่พระเจ้า เช่นเดียวกับพระนามของพระองค์

คำสรรเสริญของพระองค์ก็ไปถึงสุดปลายแผ่นดินโลก

พระหัตถ์ขวาของพระองค์บริบูรณ์ด้วยความชอบธรรม

11ภูเขาศิโยนชื่นชมยินดี ชาวยูดาห์ปลื้มปีติ

เนื่องด้วยการพิพากษาของพระองค์

12จงเดินรอบศิโยน ไปให้ทั่ว

นับจำนวนหอคอยในเมืองนั้น

13สังเกตดูเชิงเทิน

เที่ยวดูป้อมปราการ

เพื่อท่านจะได้เล่าให้คนรุ่นต่อไปฟัง

14เพราะว่าพระเจ้าองค์นี้ทรงเป็นพระเจ้าของเราตลอดนิรันดร์

พระองค์จะทรงเป็นผู้นำทางของเราจนถึงที่สุด

New Amharic Standard Version

መዝሙር 48:1-14

መዝሙር 48

የእግዚአብሔር ተራራ ጽዮን

ዝማሬ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤

በአምላካችን ከተማ በተቀደሰው ተራራ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባዋል።

2የምድር ሁሉ ደስታ የሆነው፣

በሰሜን በኩል48፥2 ጻፎን የሚለው የዕብራይስጡ ቃል የተቀደሰ ተራራን ወይም የሰሜንን አቅጣጫ ሊያመለክት ይችላል። በርቀት የሚታየው፣

በከፍታ ላይ አምሮ የደመቀው የጽዮን ተራራ፣

የታላቁ ንጉሥ ከተማ ነው።

3እግዚአብሔር በአዳራሾቿ ውስጥ ሆኖ፤

ብርቱ ምሽግ እንደ ሆናት አስመስክሯል።

4እነሆ፤ ነገሥታት ተባብረው መጡ፤

አንድ ላይ ሆነውም ገሠገሡ።

5አይተውም ተደነቁ፤

ደንግጠውም ፈረጠጡ።

6ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

በዚያ ብርክ ያዛቸው።

7የምሥራቅ ነፋስ የተርሴስን መርከብ እንደሚሰባብር፣

አንተ አብረከረክሃቸው።

8እንደ ሰማን፣

በሰራዊት አምላክ ከተማ፣

በአምላካችን ከተማ፣

እንዲሁ አየን፤

እግዚአብሔር ለዘላለም ያጸናታል። ሴላ

9አምላክ ሆይ፤ በቤተ መቅደስህ ውስጥ ሆነን፣

ምሕረትህን እናስባለን።

10አምላክ ሆይ፤ ምስጋናህ እንደ ስምህ፣

እስከ ምድር ዳርቻ ይዘልቃል፤

ቀኝ እጅህም ጽድቅን የተሞላች ናት።

11ስለ ፍርድህ፣

የጽዮን ተራራ ሐሤት ታድርግ፤

የይሁዳ መንደሮችም ደስ ይበላቸው።

12በጽዮን አካባቢ ተመላለሱ፤ ዙሪያዋንም ሂዱ፤

የጥበቃ ግንቦቿንም ቍጠሩ፤

13ለሚቀጥለው ትውልድ ትናገሩ ዘንድ፣

መከላከያ ዕርዶቿን ልብ ብላችሁ ተመልከቱ፤

መጠበቂያ ማማዎቿን እዩ።

14ይህ አምላክ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላካችን ነውና፤

እስከ መጨረሻው የሚመራንም እርሱ ነው።