วิวรณ์ 8 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

วิวรณ์ 8:1-13

ตราดวงที่เจ็ดและกระถางไฟทองคำ

1เมื่อพระเมษโปดกทรงแกะตราดวงที่เจ็ด ก็เกิดความเงียบงันไปในสวรรค์ราวครึ่งชั่วโมง

2และข้าพเจ้าเห็นทูตสวรรค์เจ็ดองค์ยืนอยู่ต่อหน้าพระเจ้า ทูตสวรรค์เหล่านั้นได้รับแตรเจ็ดคัน

3ทูตสวรรค์อีกองค์หนึ่งถือกระถางไฟทองคำเข้ามาและยืนที่แท่นบูชา ทูตนั้นได้รับเครื่องหอมมากมายสำหรับเผาถวายบนแท่นบูชาทองคำหน้าพระที่นั่งร่วมกับคำอธิษฐานของประชากรทั้งปวงของพระเจ้า 4ควันเครื่องหอมจากมือของทูตนั้นลอยขึ้นไปพร้อมกับคำอธิษฐานของประชากรของพระเจ้าสู่เบื้องพระพักตร์พระองค์ 5แล้วทูตนั้นนำกระถางไฟไปบรรจุไฟจากแท่นบูชาและโยนลงบนแผ่นดินโลก ทำให้เกิดเสียงฟ้าร้องกึกก้อง เสียงครืนๆ ฟ้าแลบแวบวาบ และแผ่นดินไหว

แตรทั้งเจ็ด

6จากนั้นทูตสวรรค์เจ็ดองค์ผู้ถือแตรเจ็ดคันก็เตรียมพร้อมที่จะเป่า

7ทูตสวรรค์องค์แรกเป่าแตร ลูกเห็บและไฟปนเลือดก็ถูกโยนลงมาบนแผ่นดิน หนึ่งในสามของโลกถูกเผาไป ต้นไม้มอดไหม้ไปหนึ่งในสาม และหญ้าเขียวก็ถูกไฟไหม้หมดสิ้น

8ทูตสวรรค์องค์ที่สองเป่าแตร และมีสิ่งหนึ่งเหมือนภูเขาใหญ่ที่ติดไฟลุกโชนถูกโยนลงทะเล หนึ่งในสามของทะเลกลายเป็นเลือด 9หนึ่งในสามของสิ่งมีชีวิตในทะเลตายสิ้น หนึ่งในสามของเรือทั้งหลายถูกทำลายไป

10ทูตสวรรค์องค์ที่สามเป่าแตรและดาวใหญ่ดวงหนึ่งที่ติดไฟลุกโชติช่วงดั่งคบเพลิงก็ตกจากท้องฟ้าลงบนหนึ่งในสามของแม่น้ำทั้งหลายและลงบนบ่อน้ำพุต่างๆ 11ดาวดวงนั้นชื่อว่าบอระเพ็ด8:11 หรือความขม ทำให้หนึ่งในสามของน้ำมีรสขมและผู้คนมากมายล้มตายไปเนื่องจากน้ำกลายเป็นน้ำขม

12ทูตสวรรค์องค์ที่สี่เป่าแตร หนึ่งในสามของดวงอาทิตย์ ดวงจันทร์ และดวงดาวต่างๆ ถูกทำลายลงจนมืดไป ทำให้เวลาหนึ่งในสามของกลางวันและกลางคืนไม่มีแสงสว่าง

13ขณะที่ข้าพเจ้าเฝ้าดูก็ได้ยินเสียงนกอินทรีบินไปกลางอากาศร้องเสียงดังว่า “วิบัติ! วิบัติ! วิบัติแก่ชาวโลกเพราะเสียงแตรที่ทูตสวรรค์อีกสามองค์กำลังจะเป่า!”

New Amharic Standard Version

ራእይ 8:1-13

ሰባተኛው ማኅተምና የወርቁ ጥና

1በጉ ሰባተኛውን ማኅተም በፈታ ጊዜ፣ ግማሽ ሰዓት ያህል በሰማይ ዝምታ ሆነ።

2ከዚያም በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፤ ሰባት መለከትም ተሰጣቸው።

3ሌላም መልአክ የወርቅ ጥና ይዞ መጣና በመሠዊያው አጠገብ ቆመ፤ እርሱም በዙፋኑ ፊት ባለው የወርቅ መሠዊያ ላይ ከቅዱሳን ጸሎት ሁሉ ጋር እንዲያቀርበው ብዙ ዕጣን ተሰጠው። 4የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ። 5መልአኩም ጥናውን ይዞ የመሠዊያውን እሳት ሞላበትና ወደ ምድር ወረወረው፤ ነጐድጓድ፣ ድምፅ፣ መብረቅና የምድር መናወጥ ሆነ።

ሰባቱ መለከቶች

6ከዚያም ሰባቱን መለከት የያዙት ሰባቱ መላእክት ለመንፋት ተዘጋጁ።

7የመጀመሪያው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ደም የተቀላቀለበት በረዶና እሳት ወደ ምድር ተጣለ፤ የምድር አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የዛፎችም አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የለመለመውም ሣር ሁሉ ተቃጠለ።

8ሁለተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ትልቅ ተራራ የሚመስል ነገር በእሳት እየተቀጣጠለ ወደ ባሕር ተጣለ፤ የባሕሩ አንድ ሦስተኛ ወደ ደም ተለወጠ፤ 9በባሕሩም ውስጥ ከሚኖሩት ሕያዋን ፍጡራን አንድ ሦስተኛ ሞተ፤ የመርከቦችም አንድ ሦስተኛ ወደመ።

10ሦስተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ እንደ ችቦ የሚነድድ ታላቅ ኮከብ በወንዞች አንድ ሦስተኛና በውሃ ምንጮች ላይ ከሰማይ ወደቀ፤ 11የኮከቡም ስም “እሬቶ8፥11 ምሬት ማለት ነው።” ይባል ነበር። የውሃውም አንድ ሦስተኛ መራራ ሆነ፤ ውሃው መራራ ከመሆኑ የተነሣም ብዙ ሰዎች ሞቱ።

12አራተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ የብርሃናቸው አንድ ሦስተኛ ይጨልም ዘንድ፣ የፀሓይ አንድ ሦስተኛ፣ የጨረቃም አንድ ሦስተኛ፣ የከዋክብትም አንድ ሦስተኛ ተመታ፤ የቀንም አንድ ሦስተኛ፣ የሌሊቱም አንድ ሦስተኛ ብርሃን እንዳይሰጥ ተከለከለ።

13ከዚያም ተመለከትሁ፤ አንድ ንስር በሰማይ መካከል ይበርር ነበር፤ በታላቅ ድምፅም፣ “የቀሩት ሦስቱ መላእክት መለከት ስለሚነፉ፣ በምድር ላይ ለሚኖሩት ወዮላቸው! ወዮላቸው! ወዮላቸው!” ሲል ሰማሁ።