Titovi 2 – SNC & NASV

Slovo na cestu

Titovi 2:1-15

Pro každého vhodný pokyn

1Veď své posluchače k tomu, co odpovídá zdravému učení: 2starší muži ať jsou střídmí a vážní, zdraví ve víře, lásce a trpělivosti. 3Podobně starší ženy ať se chovají důstojně, nepomlouvají a neholdují alkoholu. Mladším ženám mají být vychovatelkami k dobrému, 4aby milovaly své muže a děti, 5ovládaly své nálady, pečovaly o čistotu těla i duše, pořádně vedly domácnost, byly laskavé a povolné k manželům, aby nezavdaly příčinu ke kritice křesťanské víry.

6Také mladé muže veď k sebeovládání. 7Buď jim vzorem správného jednání po všech stránkách. 8Všechno, čemu učíš, ať je výstižné a odpovídá pravdě, aby protivník neměl co namítnout.

9Podřízení ať poslouchají své představené, ať jsou úslužní, neodmlouvají, 10nepodvádějí a ve všem ať je na ně naprosté spolehnutí. Tak budou vzbuzovat zájem o víru v našeho Zachránce, Boha. 11On ukázal, že miluje všechny lidi a chce je zachránit. 12To nás vede k tomu, abychom se zřekli bezbožnosti a tělesných choutek a žili své dny moudře, spravedlivě a v úctě před Bohem. 13Před námi přece leží věčná radost; vždyť očekáváme, že se ukáže ve své slávě náš veliký Bůh a Zachránce, Ježíš Kristus. 14On se za nás obětoval, abychom už nepodléhali moci hříchu a stali se jeho lidem, nadšeným pro vše dobré.

15Tak lidi uč, naléhavě přesvědčuj a napravuj, kde bude třeba. Nikdo ať tě nebere na lehkou váhu.

New Amharic Standard Version

ቲቶ 2:1-15

1አንተ ግን ከትክክለኛው ትምህርት ጋር ተስማሚ የሆነውን አስተምር። 2አረጋውያን ጭምቶች፣ የተከበሩ፣ ራሳቸውን የሚገዙና በእምነት፣ በፍቅርና በትዕግሥት ጤናማነት ያላቸው እንዲሆኑ ምከራቸው።

3እንዲሁም አሮጊቶች በአኗኗራቸው የተከበሩ እንዲሆኑ፣ በጎ የሆነውን የሚያስተምሩ እንጂ የሰው ስም የሚያጠፉ ወይም በወይን ጠጅ ሱስ የተጠመዱ እንዳይሆኑ አስተምራቸው። 4እንዲህ ከሆኑ፣ ወጣት ሴቶች ባሎቻቸውንና ልጆቻቸውን እንዲወድዱ ማስተማር ይችላሉ፤ 5የእግዚአብሔር ቃል በማንም ዘንድ እንዳይሰደብ ራሳቸውን የሚገዙና ንጹሓን፣ በቤት ውስጥ በሥራ የተጠመዱ፣ ቸሮች፣ ለባሎቻቸው የሚገዙ እንዲሆኑ ያስተምሯቸው።

6እንዲሁም ወጣት ወንዶች ራሳቸውን እንዲገዙ ምከራቸው። 7በማንኛውም ነገር መልካም የሆነውን ነገር በማድረግ ራስህን አርኣያ አድርገህ አቅርብላቸው። በምታስተምራቸውም ትምህርት ጭምተኛነትን፣ ቁም ነገረኛነትን፣ 8የማይነቀፍ ጤናማ አነጋገርንም አሳይ፤ ይኸውም ተቃዋሚ ስለ እኛ የሚናገረውን መጥፎ ነገር በማጣት እንዲያፍር ነው።

9ባሮች ለጌቶቻቸው በማንኛውም ነገር እንዲገዙ፣ ደስ እንዲያሰኟቸውና የዐጸፋ ቃል እንዳይመልሱላቸው አስተምር፤ 10አይስረቁ፤ ይኸውም በሁሉም መንገድ የአዳኛችን የእግዚአብሔር ትምህርት ይወደድ ዘንድ ፍጹም ታማኝ መሆናቸውን እንዲያስመሰክሩ ነው።

11ድነት የሚገኝበት የእግዚአብሔር ጸጋ ለሰዎች ሁሉ ተገልጧልና፤ 12ይህም ጸጋ በኀጢአት መኖርንና ዓለማዊ ምኞትን ክደን፣ በአሁኑ ዘመን ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ፣ በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት እንድንኖር ያስተምረናል፤ 13ይህም የተባረከ ተስፋችን የሆነውን የታላቁን የአምላካችንንና የአዳኛችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ በመጠባበቅ ነው፤ 14እርሱም ከክፋት ሊቤዠን፣ መልካም የሆነውን ለማድረግ የሚተጋውን የእርሱ የሆነውን ሕዝብም ለራሱ ያነጻ ዘንድ ራሱን ስለ እኛ ሰጥቷል።

15እንግዲህ ልታስተምር የሚገባህ እነዚህን ነው፤ በሙሉ ሥልጣን ምከር፤ ገሥጽም፤ ማንም አይናቅህ።