1. Солуњанима 1 – NSP & NASV

New Serbian Translation

1. Солуњанима 1:1-10

Верност Господу

Увод

1Од Павла, Силвана и Тимотеја, цркви у Солуну – вама који сте у Богу Оцу и Господу Исусу Христу: милост вам и мир.

Захвалност за веру Солуњана

2Увек захваљујемо Богу за све вас, помињући вас у својим молитвама. Непрестано се, 3пред Богом, Оцем нашим, сећамо ваше плодоносне вере, трудом исказане љубави, и постојаности ваше наде у Господа нашег Исуса Христа.

4Знамо, наиме, од Бога, вољена браћо, да вас је Бог изабрао, 5јер вам нисмо само речима навестили Радосну вест, већ силом и деловањем Духа Светога, и са потпуним уверењем. Знате и сами да смо се тако владали међу вама вас ради. 6Ви сте се тако угледали на нас и на Христа, прихватајући поруку са радошћу Духа Светог, упркос многим невољама. 7Тиме сте постали пример свим верујућима у Македонији и Ахаји. 8И не само да је реч Божија преко вас одјекнула по Македонији и Ахаји, већ се и глас о вашој вери проширио посвуда. Зато нема потребе да о томе било шта говоримо, 9јер они сами причају о томе како смо вам приступили, и како сте се окренули Богу од идола, да служите живом и истинитом Богу, 10те како очекујете долазак Сина његовог с небеса, кога је он подигао из мртвих – Исуса који нас избавља од долазећег гнева.

New Amharic Standard Version

1 ተሰሎንቄ 1:1-10

1ከጳውሎስ፣ ከሲላስና1፥1 ግሪኩ ሲልዋኑስ ይላል። ከጢሞቴዎስ፤

በእግዚአብሔር አብና በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሆኑት ለተሰሎንቄ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን፤

ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን1፥1 አንዳንድ ቅጆች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚለው የላቸውም።

ስለ ተሰሎንቄ ሰዎች እምነት የቀረበ ምስጋና

2በጸሎታችን እያስታወስናችሁ ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ስለ ሁላችሁ እናመሰግናለን። 3ከእምነት የሆነውን ሥራችሁን፣ ከፍቅር የመነጨውን ድካማችሁንና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ባላችሁ ተስፋ የተገኘውን ጽናታችሁን በአምላካችንና በአባታችን ፊት ዘወትር እናስባለን።

4በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፤ እርሱ እንደ መረጣችሁ እናውቃለን፤ 5ምክንያቱም ወንጌላችን ወደ እናንተ የመጣው በኀይልና በመንፈስ ቅዱስ፣ በብዙም መረዳት እንጂ በቃል ብቻ አይደለም። ደግሞ ስለ እናንተ ስንል በመካከላችሁ እንዴት እንደ ኖርን ታውቃላችሁ። 6እናንተ እኛንና ጌታን መስላችኋል፤ ምንም እንኳ ብርቱ መከራ ቢደርስባችሁም፣ ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ደስታ ተቀብላችኋል። 7ከዚህም የተነሣ በመቄዶንያና በአካይያ ለሚገኙ ምእመናን መልካም ምሳሌ ሆናችኋል። 8የጌታ ቃል ከእናንተ ወጥቶ በመቄዶንያና በአካይያ መሰማቱ ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ያላችሁ እምነት በሁሉ ቦታ ታውቋል፤ ስለዚህ እኛ በዚህ ጕዳይ ላይ ምንም መናገር አያስፈልገንም፤ 9በእንዴት ያለ አቀባበል እንደ ተቀበላችሁንና ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ለማገልገል ከጣዖታት ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንደ ተመለሳችሁ እነርሱ ራሳቸው ይናገራሉ፤ 10ደግሞም ከሙታን ያስነሣውንና ከሰማይ የሚመጣውን ልጁን፣ ከሚመጣውም ቍጣ የሚያድነንን ኢየሱስን እንዴት እንደምትጠባበቁ ይናገራሉ።