Псалтирь 51 – NRT & NASV

New Russian Translation

Псалтирь 51:1-11

Псалом 51

1Дирижеру хора. Наставление Давида, 2когда эдомитянин Доэг пришел к Саулу и сообщил ему: «Давид в доме Ахимелеха»51:2 См. 1 Цар. 21–22 гл..

3Что хвалишься злодейством, сильный?

Весь день со мной милость Божья!

4Твой язык замышляет гибель;

он подобен отточенной бритве, о коварный.

5Зло ты любишь больше добра

и ложь – сильнее, чем слова правды. Пауза

6Ты любишь гибельные слова

и язык вероломный.

7Но Бог погубит тебя навек;

Он схватит тебя и выкинет прочь из шатра,

исторгнет твой корень из земли живых. Пауза

8Увидят праведники и устрашатся,

посмеются над ним, говоря:

9«Вот человек,

который не сделал Бога своей крепостью,

а верил в свои сокровища

и укреплялся, уничтожая других51:9 Букв.: «своей гибелью» или «своим желанием».

10А я подобен оливе,

зеленеющей в Божьем доме,

я верю в Божью милость вовеки.

11Буду славить Тебя вовек за сделанное Тобой.

Перед Твоими верными я буду уповать на Твое имя,

потому что оно прекрасно.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 51:1-19

መዝሙር 51

የኀጢአት ኑዛዜ

ለመዘምራን አለቃ፤ ዳዊት ወደ ቤርሳቤህ ከገባ በኋላ፣ ነቢዩ ናታን ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ መጠን፣

ምሕረት አድርግልኝ፤

እንደ ርኅራኄህም ብዛት፣

መተላለፌን ደምስስ።

2በደሌን ፈጽሞ ዕጠብልኝ፤

ከኀጢአቴም አንጻኝ።

3እኔ መተላለፌን ዐውቃለሁና፤

ኀጢአቴም ዘወትር በፊቴ ነው።

4በውሳኔህ ትክክል፣

በምትሰጠው ፍርድም ንጹሕ ትሆን ዘንድ፣

አንተን፣ በርግጥ አንተን ብቻ በደልሁ፤

በፊትህም ክፉ ነገር አደረግሁ።

5ስወለድ ጀምሮ በደለኛ፣

ገና እናቴም ስትፀንሰኝ ኀጢአተኛ ነኝ።

6እነሆ፤ እውነትን ከሰው ልብ ትሻለህ፤51፥6 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

ስለዚህ ጥልቅ ጥበብን በውስጤ አስተምረኝ።51፥6 አስተምረህኛል ወይም ትፈልጋለህ ተብሎ መተርጐም ይቻላል።

7በሂሶጵ እርጨኝ፤ እኔም እነጻለሁ፤

ዕጠበኝ፤ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።

8ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፤

ያደቀቅሃቸው ዐጥንቶቼም ደስ ይበላቸው።

9ፊትህን ከኀጢአቴ መልስ፤

በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።

10አምላኬ ሆይ፤ ንጹሕ ልብ ፍጠርልኝ፤

ቀና የሆነውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።

11ከፊትህ አትጣለኝ፤

ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድ።

12የማዳንህን ደስታ መልስልኝ፤

በእሽታ መንፈስም ደግፈህ ያዘኝ።

13እኔም ለሕግ ተላላፊዎች መንገድህን አስተምራለሁ፤

ኀጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።

14የድነቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤

ደም ከማፍሰስ አድነኝ፤

አንደበቴም ስለ ጽድቅህ በእልልታ ይዘምራል።

15ጌታ ሆይ ከንፈሮቼን ክፈት፤

አፌም ምስጋናህን ያውጃል።

16መሥዋዕትን ብትወድድ ኖሮ ባቀረብሁልህ ነበር፤

የሚቃጠል መሥዋዕትም ደስ አያሰኝህም።

17እግዚአብሔር የሚቀበለው መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፤51፥17 ወይም አምላክ ሆይ፤ የእኔ መሥዋዕት የተሰበረ

እግዚአብሔር ሆይ፤

አንተ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ አትንቅም።

18በበጎ ፈቃድህ ጽዮንን አበልጽጋት፤

የኢየሩሳሌምንም ቅጥሮች ሥራ።

19የጽድቅ መሥዋዕት፣ የሚቃጠል መሥዋዕትና

ሙሉ የሚቃጠል መሥዋዕት ያን ጊዜ ደስ ያሰኙሃል፤

ኰርማዎች በመሠዊያህ ላይ የሚሠዉትም ያን ጊዜ ነው።