Micah 3 – NIVUK & NASV

New International Version – UK

Micah 3:1-12

Leaders and prophets rebuked

1Then I said,

‘Listen, you leaders of Jacob,

you rulers of Israel.

Should you not embrace justice,

2you who hate good and love evil;

who tear the skin from my people

and the flesh from their bones;

3who eat my people’s flesh,

strip off their skin

and break their bones in pieces;

who chop them up like meat for the pan,

like flesh for the pot?’

4Then they will cry out to the Lord,

but he will not answer them.

At that time he will hide his face from them

because of the evil they have done.

5This is what the Lord says:

‘As for the prophets

who lead my people astray,

they proclaim “peace”

if they have something to eat,

but prepare to wage war against anyone

who refuses to feed them.

6Therefore night will come over you, without visions,

and darkness, without divination.

The sun will set for the prophets,

and the day will go dark for them.

7The seers will be ashamed

and the diviners disgraced.

They will all cover their faces

because there is no answer from God.’

8But as for me, I am filled with power,

with the Spirit of the Lord,

and with justice and might,

to declare to Jacob his transgression,

to Israel his sin.

9Hear this, you leaders of Jacob,

you rulers of Israel,

who despise justice

and distort all that is right;

10who build Zion with bloodshed,

and Jerusalem with wickedness.

11Her leaders judge for a bribe,

her priests teach for a price,

and her prophets tell fortunes for money.

Yet they look for the Lord’s support and say,

‘Is not the Lord among us?

No disaster will come upon us.’

12Therefore because of you,

Zion will be ploughed like a field,

Jerusalem will become a heap of rubble,

the temple hill a mound overgrown with thickets.

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 3:1-12

መሪዎችና ነቢያት ተገሠጹ

1ከዚያም እኔ እንዲህ አልሁ፤

“እናንት የያዕቆብ መሪዎች፤

እናንት የእስራኤል ቤት ገዦች ስሙ፤

ፍትሕን ማወቅ አይገባችሁምን?

2መልካሙን ጠላችሁ፤ ክፉውንም ወደዳችሁ፤

የሕዝቤን ቈዳ ገፈፋችሁ፤

ሥጋቸውንም ከዐጥንቶቻቸው ለያችሁ፤

3የሕዝቤን ሥጋ በላችሁ፤

ቈዳቸውን ገፈፋችሁ፤

ዐጥንቶቻቸውንም ሰባበራችሁ፤

በመጥበሻ እንደሚጠበስ፣

በድስት እንደሚቀቀል ሥጋ ቈራረጣችኋቸው።”

4እነርሱም ወደ እግዚአብሔር ይጮኻሉ፤

እርሱ ግን አይመልስላቸውም፤

ካደረጉት ክፋት የተነሣ፣

በዚያ ጊዜ ፊቱን ከእነርሱ ይሰውራል።

5እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሕዝቤን የሚያስቱ ነቢያት፣

ሰው ሲያበላቸው፣ ‘ሰላም አለ’ ይላሉ፤

ሳያበላቸው ሲቀር ግን፣

ጦርነት ሊያውጁበት ይነሣሉ።

6ስለዚህ ሌሊቱ ያለ ራእይ፣

ጨለማውም ያለ ንግርት ይመጣባችኋል፤

በነቢያት ላይ ፀሓይ ትጠልቅባቸዋለች፤

ቀኑም ይጨልምባቸዋል።

7ባለ ራእዮች ያፍራሉ፤

ንግርተኞችም ይዋረዳሉ፤

ሁሉም ፊታቸውን ይሸፍናሉ፤

ከእግዚአብሔር መልስ የለምና።”

8እኔ ግን፣

ለያዕቆብ በደሉን፣

ለእስራኤልም ኀጢአቱን እነግር ዘንድ፣

ኀይልን በእግዚአብሔር መንፈስ፣

ፍትሕና ብርታትም ተሞልቻለሁ።

9እናንተ የያዕቆብ ቤት መሪዎች፣

እናንት የእስራኤል ቤት ገዦች፣

ፍትሕን የምትንቁ፣

ትክክለኛ የሆነውንም ነገር ሁሉ የምታጣምሙ፤ ስሙ፤

10ጽዮንን ደም በማፍሰስ፣

ኢየሩሳሌምን በክፋት የምትገነቡ፤ ስሙ።

11መሪዎቿ በጕቦ ይፈርዳሉ፤

ካህናቷ ለዋጋ ሲሉ ያስተምራሉ፤

ነቢያቷም ለገንዘብ ሲሉ ይናገራሉ።

ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ ተደግፈውም፣

እግዚአብሔር በመካከላችን አይደለምን?

ምንም ዐይነት ክፉ ነገር አይደርስብንም” ይላሉ።

12ስለዚህ በእናንተ ምክንያት፣

ጽዮን እንደ ዕርሻ ትታረሳለች፣

ኢየሩሳሌም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤

የቤተ መቅደሱም ኰረብታ ዐረም የበቀለበት ጕብታ ይሆናል።