Proverbs 9 – NIV & NASV

New International Version

Proverbs 9:1-18

Invitations of Wisdom and Folly

1Wisdom has built her house;

she has set up9:1 Septuagint, Syriac and Targum; Hebrew has hewn out its seven pillars.

2She has prepared her meat and mixed her wine;

she has also set her table.

3She has sent out her servants, and she calls

from the highest point of the city,

4“Let all who are simple come to my house!”

To those who have no sense she says,

5“Come, eat my food

and drink the wine I have mixed.

6Leave your simple ways and you will live;

walk in the way of insight.”

7Whoever corrects a mocker invites insults;

whoever rebukes the wicked incurs abuse.

8Do not rebuke mockers or they will hate you;

rebuke the wise and they will love you.

9Instruct the wise and they will be wiser still;

teach the righteous and they will add to their learning.

10The fear of the Lord is the beginning of wisdom,

and knowledge of the Holy One is understanding.

11For through wisdom9:11 Septuagint, Syriac and Targum; Hebrew me your days will be many,

and years will be added to your life.

12If you are wise, your wisdom will reward you;

if you are a mocker, you alone will suffer.

13Folly is an unruly woman;

she is simple and knows nothing.

14She sits at the door of her house,

on a seat at the highest point of the city,

15calling out to those who pass by,

who go straight on their way,

16“Let all who are simple come to my house!”

To those who have no sense she says,

17“Stolen water is sweet;

food eaten in secret is delicious!”

18But little do they know that the dead are there,

that her guests are deep in the realm of the dead.

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 9:1-18

ጠቢብነትና ተላላነት

1ጥበብ ቤቷን ሠራች፤

ሰባቱን ምሰሶዎቿንም ጠርባ አቆመች፤

2ፍሪዳዋን ዐረደች፤ የወይን ጠጇን ጠመቀች፤

ማእዷንም አዘጋጀች።

3ሴት አገልጋዮቿንም ላከች፤

ከከተማዪቱም ከፍተኛ ቦታ ተጣራች።

4እርሷም ማመዛዘን ለጐደላቸው፣

“ማስተዋል የሌላችሁ ሁሉ ወደዚህ ኑ” አለች።

5“ኑ፤ ምግቤን ተመገቡ፤

የጠመቅሁትንም የወይን ጠጅ ጠጡ።

6የሞኝነት መንገዳችሁን ተዉ፤ በሕይወት ትኖራላችሁ፤

በማስተዋልም መንገድ ተመላለሱ።”

7ፌዘኛን የሚገሥጽ ሁሉ ስድብን በራሱ ላይ ያመጣል፤

ክፉውን ሰው የሚዘልፍ ሁሉ ውርደት ያገኘዋል።

8ፌዘኛን አትዝለፈው፤ ይጠላሃል፤

ጠቢብን ገሥጸው፤ ይወድድሃል።

9ጠቢብን አስተምረው፣ ይበልጥ ጥበበኛ ይሆናል፤

ጻድቁን ሰው አስተምረው፤ ዕውቀቱን ይጨምራል።

10“የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤

ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል ነው።

11ዘመንህ በእኔ ምክንያት ይረዝማልና፤

ዕድሜም በሕይወትህ ላይ ይጨመርልሃል።

12ጠቢብ ብትሆን ጥበበኛነትህ ለራስህ ነው፤

ፌዘኛ ብትሆን የምትጐዳው ያው አንተው ነህ።”

13ጥበብ የለሽ ሴት ለፍላፊ ናት፤

እርሷም ስድና ዕውቀት የለሽ ናት።

14በቤቷ ደጃፍ ላይ ትጐለታለች፤

በከተማዪቱ ከፍተኛ ቦታ በመቀመጫ ላይ ትቀመጣለች።

15በዚያ የሚያልፉትን፣

መንገዳቸውን ይዘው የሚሄዱትን ትጣራለች።

16እርሷም ማመዛዘን ለጐደላቸው፣

“ማስተዋል የሌላችሁ ሁሉ ወደዚህ ኑ” ትላለች።

17“የስርቆት ውሃ ይጣፍጣል፤

ተሸሽገው የበሉት ምግብ ይጥማል።”

18እነርሱ ግን ሙታን በዚያ እንዳሉ፣

ተጋባዦቿም በሲኦል9፥18 ወይም መቃብር ጥልቀት ውስጥ እንደ ሆኑ አያውቁም።