Isaiah 18 – NIV & NASV

New International Version

Isaiah 18:1-7

A Prophecy Against Cush

1Woe to the land of whirring wings18:1 Or of locusts

along the rivers of Cush,18:1 That is, the upper Nile region

2which sends envoys by sea

in papyrus boats over the water.

Go, swift messengers,

to a people tall and smooth-skinned,

to a people feared far and wide,

an aggressive nation of strange speech,

whose land is divided by rivers.

3All you people of the world,

you who live on the earth,

when a banner is raised on the mountains,

you will see it,

and when a trumpet sounds,

you will hear it.

4This is what the Lord says to me:

“I will remain quiet and will look on from my dwelling place,

like shimmering heat in the sunshine,

like a cloud of dew in the heat of harvest.”

5For, before the harvest, when the blossom is gone

and the flower becomes a ripening grape,

he will cut off the shoots with pruning knives,

and cut down and take away the spreading branches.

6They will all be left to the mountain birds of prey

and to the wild animals;

the birds will feed on them all summer,

the wild animals all winter.

7At that time gifts will be brought to the Lord Almighty

from a people tall and smooth-skinned,

from a people feared far and wide,

an aggressive nation of strange speech,

whose land is divided by rivers—

the gifts will be brought to Mount Zion, the place of the Name of the Lord Almighty.

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 18:1-7

በኢትዮጵያ ላይ የተነገረ ትንቢት

1በኢትዮጵያ ወንዞች ዳር ለምትገኝ፣

ፉር ፉር የሚሉ ክንፎች ላሉባት18፥1 ወይም፣ አንበጣ ማለት ነው። ምድር ወዮላት!

2ይህችውም መልእክተኞችን በባሕር፣

ከወንዞች ማዶ በደንገል ጀልባ የምትልክ ናት።

እናንት ፈጣን መልእክተኞች

ረዣዥምና ቈዳው ወደ ለሰለሰ፣

ከቅርብም ከሩቅም ወደሚፈራ ሕዝብ፣

ኀያልና ቋንቋው ወደማይገባ፣

ወንዞች ምድሩን ወደሚከፍሉት መንግሥት፣ ሂዱ!

3እናንት የዓለም ሕዝቦች፣

በምድርም የምትኖሩ ሁሉ፣

በተራሮች ላይ ምልክት ሲሰቀል ታዩታላችሁ፤

መለከትም ሲነፋ ትሰሙታላችሁ።

4እግዚአብሔር እንዲህ ብሎኛል፤

“ጸጥ ብዬ እቀመጣለሁ፤

ከማደሪያዬም በፀሓይ ሐሩር እንደሚያስፈልጋችሁ ብርቅርቅ ትኵሳት፣

በመከርም ሙቀት እንደ ደመና ጠል ሆኜ እመለከታለሁ።”

5ከመከር በፊት የአበባው ወቅት ሲያልፍ፣

አበባው የጐመራ የወይን ፍሬ ሲሆን፣

የወይን ሐረጉን ተቀጥላ በመግረዣ ይገርዘዋል፤

የተንሰራፋውንም ቅርንጫፍ ቈራርጦ ያስወግደዋልና።

6ሁሉም በተራራ ላይ ለሚኖሩ ነጣቂ አሞሮች፣

ለዱርም አራዊት ይተዋሉ፤

አሞሮች በጋውን ሁሉ ሲበሉት ይባጃሉ፤

የዱር አራዊትም ክረምቱን ሁሉ ሲበሉት ይከርማሉ።

7በዚያን ጊዜ ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር

ረዣዥምና ቈዳው ከለሰለሰ፣

ከቅርብም ከሩቅም ከሚፈራ ሕዝብ፣

ኀያልና ቋንቋው ከማይገባ፣

ወንዞችም ምድሩን ከሚከፍሉት መንግሥት፣ ገጸ በረከት ይመጣለታል፤

ገጸ በረከቱም የሚመጣለት የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ስም ወዳለበት ወደ ጽዮን ተራራ ነው።