مزمور 93 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 93:1-5

الْمَزْمُورُ الثَّالِثُ وَالتِّسْعُونَ

1الرَّبُّ قَدْ مَلَكَ مُرْتَدِياً الْجَلالَ. مُتَنَطِّقاً بِحِزَامِ الْقُوَّةِ. الأَرْضُ تَثَبَّتَتْ فَلَنْ تَتَزَعْزَعَ. 2عَرْشُكَ ثَابِتٌ مُنْذُ الْقَدِيمِ، لأَنَّكَ اللهُ مُنْذُ الأَزَلِ. 3يَا رَبُّ قَدْ رَفَعَتِ الأَنْهَارُ صَوْتَهَا. تَرْفَعُ الأَنْهَارُ صَوْتَ مَوْجِهَا الْهَادِرِ. 4الرَّبُّ فِي الْعَلاءِ أَعْظَمُ مِنْ صَوْتِ الْمِيَاهِ الْغَزِيرَةِ وَمِنْ أَمْوَاجِ الْبَحْرِ الْهَائِلَةِ. 5أَقْوَالُكَ ثَابِتَةٌ إِلَى الأَبَدِ، وَبِبَيْتِكَ أَيُّهَا الرَّبُّ تَلِيقُ الْقَدَاسَةُ مَدَى الدَّهْرِ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 93:1-5

መዝሙር 93

የእግዚአብሔር ግርማ

1እግዚአብሔር ነገሠ፤ ግርማንም ተጐናጸፈ፤

እግዚአብሔር ግርማን ለበሰ፤

ብርታትንም ታጠቀ፤

ዓለም እንዳትናወጥ ጸንታለች፤

ማንም አይነቀንቃትም።

2ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የጸና ነው፤

አንተም ከዘላለም እስከ ዘላለም አለህ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ወንዞች ከፍ አደረጉ፤

ወንዞች ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ፤

ወንዞች የሚያስገመግም ማዕበላቸውን ከፍ አደረጉ።

4ከብዙ ውሆች ድምፅ ይልቅ፣

ከባሕርም ሞገድ ይልቅ፣

ከፍ ብሎ ያለው እግዚአብሔር ኀያል ነው።

5ሥርዐትህ የጸና ነው፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ ዘላለሙ፣

ቤትህ በቅድስና ይዋባል።