مزمور 7 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 7:1-17

الْمَزْمُورُ السَّابِعُ

قَصِيدَةُ حُزْنٍ نَظَمَهَا دَاوُدُ وَرَنَّمَهَا لِلرَّبِّ رَدّاً لِلتُّهْمَةِ الَّتِي رَمَاهُ بِها كُوشُ الْبَنْيَامِينِيُّ

1أَيُّهَا الرَّبُّ إِلَهِي، إِلَيْكَ الْتَجَأْتُ، فَأَنْقِذْنِي وَنَجِّنِي مِنْ جَمِيعِ مُطَارِدِيَّ، 2لِئَلّا يَفْتَرِسَ الْعَدُوُّ نَفْسِي كَالأَسَدِ، وَلَيْسَ مَنْ يُنْقِذُنِي.

3أَيُّهَا الرَّبُّ إِلَهِي، إِنْ كُنْتُ قَدِ اقْتَرَفْتُ هَذِهِ الإِسَاءَةَ، وَكَانَتْ يَدَايَ قَدِ ارْتَكَبَتَا هَذَا الإِثْمَ، 4إِنْ كُنْتُ قَدْ أَسَأْتُ لِمَنْ أَحْسَنَ إِلَيَّ وَسَلَبْتُ عَدُوِّي مِنْ غَيْرِ سَبَبٍ، 5إِذَنْ فَلْيُطَارِدِ الْعَدُوُّ نَفْسِي ويَنْزِعْهَا مِنِّي، وَلْيَدُسْ فِي الأَرْضِ حَيَاتِي، وَيُعَفِّرْ فِي التُّرَابِ شَرَفِي.

6انْهَضْ يَا رَبُّ فِي احْتِدَامِ غَضَبِكَ، وَانْتَصِبْ فِي وَجْهِ سَخَطِ خُصُومِي، يَا مَنْ أَوْصَيْتَ بِالْعَدْلِ. 7لِتُحِطْ بِكَ جَمَاعَةُ الشُّعُوبِ فَتَحْكُمَهَا مِنْ مَنَصَّةِ الْقَضَاءِ الْعَالِيَةِ. 8إِنَّ الرَّبَّ يَدِينُ الأُمَمَ. اقضِ لِي يَا رَبُّ كَحَقِّي، بِحَسَبِ مَا فِيَّ مِنْ كَمَالٍ. 9ضَعْ حَدّاً لِشَرِّ الأَشْرَارِ، وَأَثْبِتْ بَرَاءَةَ الأَبْرَارِ، أَيُّهَا الإِلَهُ الْعَادِلُ فَاحِصُ الْقُلُوبِ وَالدَّخَائِلِ. 10مَلْجَإِي عِنْدَ اللهِ مُخَلِّصِ مُسْتَقِيمِي الْقُلُوبِ.

11اللهُ قَاضٍ عَادِلٌ، وَهُوَ إِلَهٌ يَسْخَطُ عَلَى الأَشْرَارِ فِي كُلِّ يَوْمٍ. 12صَقَلَ سَيْفَهُ لِيَضْرِبَ بِهِ الشِّرِّيرَ الَّذِي لَا يَتُوبُ. وَتَّرَ قَوْسَهُ وَهَيَّأَهَا. 13أَعَدَّ لَهُ الأَسْلِحَةَ الْقَتَّالَةَ، وَجَعَلَ سِهَامَهُ مُحْرِقَةً.

14هُوَذَا الْعَدُوُّ يَتَمَخَّضُ بِالإِثْمِ، يَحْبَلُ بِالأَذَى، وَيَلِدُ كَذِباً. 15حَفَرَ بِئْراً وَعَمَّقَهَا، فَسَقَطَ فِيهَا. 16شَرُّهُ يَرْتَدُّ عَلَى رَأْسِهِ، وَظُلْمُهُ يَهْبِطُ عَلَى هَامَتِهِ. 17إِنِّي أَحْمَدُ الرَّبَّ مِنْ أَجْلِ عَدَالَتِهِ، وَأَتَرَنَّمُ لاسْمِ الرَّبِّ العَلِيِّ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 7:1-17

መዝሙር 7

በስደት ጊዜ የጻድቁ ሰው ጸሎት

ዳዊት በብንያማዊው በኩዝ ምክንያት ለእግዚአብሔር የዘመረው መዝሙር።

1እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ አንተ መሸሸጊያዬ ነህ፤

ከሚያሳድዱኝ ሁሉ አድነኝ፤ ታደገኝም፤

2አለዚያ እንደ አንበሳ ይዘነጣጥሉኛል፤

የሚያድነኝ በሌለበትም ይቦጫጭቁኛል።

3እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ይህን አድርጌ ከሆነ፣

በደልም በእጄ ከተገኘ፣

4በጎ ለዋለልኝ ክፉ መልሼ ብሆን፣

ጠላቴንም በከንቱ ዘርፌ ከሆነ፣

5ጠላቴ አሳድዶ ይያዘኝ፤

ሕይወቴን ከምድር ይቀላቅል፤

ክብሬንም ከዐፈር ይደባልቅ። ሴላ

6እግዚአብሔር ሆይ፤ በመዓትህ ተነሥ፤

በቍጣ በተነሡብኝ ላይ ተነሥ፤

አምላኬ ሆይ፤ ንቃ፤ ትእዛዝም አስተላልፍ!

7የሕዝቦች ጉባኤ ይክበብህ፤

አንተም ከላይ ሆነህ ግዛቸው፤

8እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ይፈርዳል።

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ጽድቄ ፍረድልኝ፤

ልዑል ሆይ፤ እንደ ቅን አካሄዴ መልስልኝ።

9ልብንና ኵላሊትን የምትመረምር፣

ጻድቅ አምላክ ሆይ፤

የክፉዎችን ዐመፅ አጥፋ፤

ጻድቁን ግን አጽና።

10ጋሻዬ7፥10 ወይም የእኔ ልዑል ልዑል አምላክ ነው፤

እርሱ ልበ ቅኖችን ያድናቸዋል።

11እግዚአብሔር ጻድቅ ዳኛ ነው፤

ቍጣውንም በየዕለቱ የሚገልጥ አምላክ ነው።

12ሰው በንስሓ የማይመለስ ከሆነ ግን፣

ሰይፉን7፥12 ወይም ሰው ንስሓ ካልገባ፣ እግዚአብሔር ሰይፉን ይስላል፤

ቀስቱን ይገትራል።

13የሚገድሉ ጦር ዕቃዎቹን አሰናድቷል፤

የሚንበለበሉትን ፍላጻዎቹንም አዘጋጅቷል።

14ክፋትን እያማጠ ያለ ሰው፣

ቅጥፈትን አርግዞ፣ ሐሰትን ይወልዳል።

15ጕድጓድ ምሶ ዐፈሩን የሚያወጣ፣

በአዘጋጀው ጕድጓድ ራሱ ይገባበታል።

16ተንኰሉ ወደ ራሱ ይመለሳል፤

ዐመፃውም በገዛ ዐናቱ ላይ ይወርዳል።

17ስለ ጽድቁ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀርባለሁ፤

የልዑል እግዚአብሔርን ስም በመዝሙር አወድሳለሁ።